በአለማየሁ ጥበቡ
ክፍል አንድ
በምንም ተከሰስ ከመታሰር አትድንም ፡፡ ህግና ህገመንግስት በወረቀት ላይ ቢኖርም በትክክል አይሰራበትም ላም አለኝ
በሰማይ ልትለው ትችላለህ ፈፅሞ እንዳታስብ ሰባዊ መብት ምን እንደሆን እዚህ ምድር ላይ አይታወቅም ፡፡በየጉራንጉሩ
ያሉ እስርቤት ሳይሆኑ መታጎርያ ቤቶች ቁጥራቸው ሀገሪቱ ላይ ካሉ ሆስፒታሎችና መስርያ ቤቶች ይበልጣሉ፡፡ በነዚህ
መታጎርያ ቤቶች ታስሮ ምንም ሳይሆን ከነጤናው የወጣ ሰው በጣም እድለኛ ምናልባትም የፈጣሪ ሸሪክ ነው ፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ እስር ቤቶች በሁለት ይከፈላሉ እነሱም ፡-
1...ፈዴራል መንግስት ስር ያሉ እስር ቤቶች 1.
- ቃሊቲ ማረምያ ቤት
- ዝዋይ ማረምያ ቤት
-ሸዋ ሮቢት ማረምያ ቤት
- ድሬደዋ ማረምያ ቤት
2... በክልል መንግስት ስር ያሉ ቁጥራቸው የትየለሌ የሆኑ እስር ቤቶች ናቸው 2.
አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሰራም ያልሰራም ቢሆን ብቻ የመታሰር እጣ የወጣበት ሰው እንደወንጀሉ የሚታሰርበት ቦታ
ይለያያል ከዚህ በታች ያሉት እስር ቤቶች ጊዛዊ እስር ቤቶች ናቸው ፡፡ከፍተኛው ፍርድ ቤት /ልደታ ያለው ከፍተኛ ችሎት /
እስክትቀርብ ድረስ ጊዛዊ ምርመራ የሚደረግባቸው ናቸው
/ ሀ ፤ለ እና ሐ በደንብ ተመልከት/
ሀ.... ለምሳሌ ጫማ ሲሰርቅ የተያዘ ሰው /የአንድ እግር ጫማም ሊሆን ይችላል/ የሚታሰረው በየቀበሌው ባለ እስር ቤት ነው ፡
፡ቀላል ወንጀሎች ስርቆት፤ስድድቦሽ ፤ወዘተ እንደወንጀላቸው መጠን በየወረዳው ባሉ ዳኞች ይዳኛሉ ፡፡ ዋስ ቶሎ ያገኛሉ
ይገባሉ ይወጣሉ ይህ አይነቱ ወንጀል እና ወንጀለኛ መንግስትን ፈፅሞ አሳስቦት አያቅም ፡፡
ለ.... ወንጀሉ ከበድ ያለነው ከተባለ ለምሳሌ ሰው መግደል ፤ከባባድ ስርቆቶች ፤አስገድዶ መድፈር፤ በቼክ ሰውን ማጭበርበር ፤
ከባባድ ማታለሎች ወዘተ የመሰሉት ወንጀሎች ላይ የተሰማራ ሰው የሚታሰረው ሶስተኛ የሚባለው እስርቤት ነው ይህ እስር
ቤት ግማሽ አካሉን ለማእከላዊ ሰጥቶ ፕያሳ ምድር ላይ የሚገኝ ዘግናኝ እና አስፈሪ እስር ቤት ነው ፡፡ ያረከውንም
ያላረከውንም በዱላ ብዛት የምታምነበት ቤት ይሄ ነው፡፡ በቀላል በበሩ ትገባለህ መውጫዋን ግን አታቀውም፡፡ በትንሹ
ምርመራ ላይ እስከ ስድስት ወር ልትቆይ ትችላለህ፡፡ለይስሙላ ፍርድ ቤት ይወስዱሀል ያመጡሀል ምክንያቱም ህገ
መንግስቱ ላይ
አንቀጽ 19 /የተያዙ ሰዎች መብት/
ቁጥር 3 ‹‹የተያዙ ሰዎች በአርባ ስምንት ሰአት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አላቸው ፡፡››
ይላል ስለዚህ ትሄዳለህ መርማሪው ምርመራዬን አለጨረስኩም ተጨማሪ ቀን ይሰጠኝ ይላል ዳኛውም የተቀመጠው ለዚሁ
ነው ተጨማሪ ቀን በደንብ ይሰጠዋል፡፡በደንብ ትታሻለህ መረጃው ሲደልብ ከፍተኛ ፍርድቤት ፋይልህ ይላካል አቃቢ ህግ
ጥሩ አንቀፅ ከፍቶ ዳኛ ፊት ያቀርብሀል፡፡ በስድስት ወር ምርመራ ምንም ካላገኙብህ በነፃና ካሳ ሰጥተው አይሸኙህም እንዲህ ካደረጉማ ኢትዮጵያም ትከስራለች ሀገሪቷ ላይም ህግ የለም ይባላል ስለዚህ በመታወቅያ ዋስ ይፈቱሀሀል ይህ ማለት ምን
ማለት ነው እስከግዜው ተፈተሃል ማለት ነው፡፡
ሐ.. . . ሌላኛው እስር ቤት ማዕከላዊ የሚባለው ነው
ከመንግስት ጋር ተቃርነሃል? የሀገርን ጥቅም እነሱ እንደሚሉት ለሌላ ሀገር አጋልጠሀል ?ፖለቲከኛነት ተጠናውቶሀል ? እቺን
የጥጋብና የፈንጠዝያ ሀገር ደሃ ናት ብለሃል? የዜጎች መብት አለተከበረም ብለሀል ? የመናገር መብቴ ይከበርልኝ ብለሀል?
ጠንካራ የፖለቲካ ድርጅት አቋቁመሀል ?
በነፃ ፕሬስ አለ ባይነት መንግስትን ወይ ባለስልጣኑን ተችተሀል? እነዚህንና የነዚህን ተዛማች ተግባሮችን ካረክ የትም
አትታሰርም እድሜ ለማዕከላዊ እስር ቤት ፡፡ ምርመራህ እስኪያልቅና ወደ ከፍተኛው ፍርድ ቤት እስትቀርብ ጥፍርህ
ይነቀላል ብልትህ ይመግላል አካልህ በዱላ ብዛት ይበጣጠሳል ቶርች ትገለበጣለህ ይሄ ሁሉ እናት ሀገርህ ምድር ላይ ነው
የሚሆነው ያውም ባንተው ዜጎች ፡፡
በ ሀእና ለ /የ ሐ አላቅም/ እስር ቤቶች ካቦዎች አሉ /እስረኛን የሚያስተዳድሩ እስረኞች / እንደገባህ ያስቀምጡህ እና በምን
እንደታሰርክ ይጠይቁህ እና አይዞህ ብለው የቤት መዋጮ ስጥ ይሉሀል ካለህ እስከ ሶስት መቶም ልትሰጥ ትችላለህ ይሄ ብር
ልቃ አጣቢዎች ለቤት አፅጂዎች ለሽንት ደፊ ቅጥረኛ እስረኞች የሚሰጥ ነው ይልሀል ካቦው ፡፡ ሽንት ዲፋዎች ማለት
እስረኞቹ ለሊት በትልቅ ባሊ ሲሸኑ ያደሩትን ሽንት መደፋ ማለትነው ለዚህም አገልግሎቱ ይከፈለዋል፡፡ ካቦው ሲጠይቅህ
ገንዘብ ከሌለህና ጠያቂህ ሲመጣ ተቀብለህ የማትሰጥ ከሆነ እስረኛው የበላበትን እቃ ታጥባለህ ሽንት ትደፋለህ ቤት
ታፀዳለህ ይሄን እናዳታደርግ ከ 50 ብር ጀምሮ ለካቦው ስጠው ፡፡ካቦው ተሰሚነት አለው፡፡ከሱ ጋር መጣላት የለብህም፡፡
እንግዲህ ከሶስቱም እስር ቤቶች ማለትም ከ ሀ፤ለ እና ሐ ግዚያዊ እስር ቤቶች ምርመራህን ጨርሰህ ወደ ከፍተኛ ፍርድ
ቤት ከቀረብክ በኃላ በዛኑ ቀን አልያም በማግስቱ ወደ ቃሊቲ ማረምያ ቤት ትላካለህ እድለኛ ከሆንክ ፤ገንዘብ ካለህ ፤ ጥሩ
ዘመድ ካለህ ምንም ወንጀል ስራ ‹‹ ገንዘብ ሲናገር ህግ ዝም ይላል›› ይባላል ከነተረቱ ስለዚህ ዋስትና ይፈቀድልህና ቃሊቲ
ሳትወርድ ከውጪ ሆንሀ ክስህን ትከታተላለህ ፡፡ የኔ ብጤው ምስኪን ይህን እድል በጆሮው ከመስማት በቀር ሆኖለት
አያቅም ቃሊቲ መውረድ ግድ ነው፡፡
ቃሊቲ ማረምያ ቤት /የፈዴራል መንግስት እስር ቤት/
የሚገኘው ቃሊቲ ነው ፡፡ በሰፊ መሬት ላይ የተሰራ ሲሆን አሁን ያለው መመንግስት ነው የሰራው ፡፡ ደፋር እስረኛ ካለ አጥሩ
አያሳስብም ህብረት ካለ እስር ቤቱ ለማምለጥ ቀላል ነው ፡፡ ግን ህብረት የለም አንድነት በዘፈን ካልሆነ አይታወቅም አንዱ
አንዱን ይፈራል ፡፡እንዴት አንፈራራ ? በስንት ዱላ እና ቶርች ከግዚያዊ እስር ቤት ወደዚህ የመጣ ምስኪን ታሳሪ ባይፈራ
አይገርምም ፡፡
ቃሊቲ ብዙ ዞኖች አሉት ዝሆን ስል እንስሳውን እንዳይመስልህ ቀጠናዎች /ግቢዎች /አሉት በአንዱ ቃሊቲ ውስጥ ሌላ
ስድስት ወይ ሰባት ግቢዎች አሉት እያልኩህ ነው፡፡ አንደኛው ጊቢ የሴቶች ክልል የሚባለው ሲሆን የተቀሩት የዎንዶች ነው
እኔ ከቃሊቲ ልለቅ አካባቢ ሌላም ዞኖዎች ሳይጨመር አይቀርም ፡፡ትንንሽ ግቢዎችም እንዳሉት ሰምቼያለሁ፡፡በአንድ ቀን
ግቢውን ዞረህ አጨርሰውም፡፡
ከሀ፤ከለ፤ከሐ ጊዛዊ እስር ቤቶች ወደ ቃሊቲ በመኪና ትወሰዳለህ ግቢው ጋ ስትደርስ አጥሩ የሽቦ ሆኖ በሩ በትልቅ ግንብ
የተሰራ ነው በትላቅ አርማም ቃሊቲ ማረምያ ቤት የሚል ከበሩ ላይ ተሰቀሏል ፡፡ እንደገባህ ከመኪና እየሰደቡና እየገላመጡ
ትወርዳለህ ስትወርድ ደሳሳ ቢሮዎች ትልልቅ እንጨት የያዙ ቦታዎች ታያለህ ይህ በስተቀኝ እና ፊት ለፊት ያለ ሲሆን
በስተግራ ያንበሳ አጥር የመሰለ በሽቦ አጥር የተከለለ ቦታ ታያለህ አይዞህ እዚህ ውስጥ አትታሰርም ይሄ የታጠረ ቦታ
በቀጠሮህ ቀን ፍርድቤት ልትሄድ ስትል የምትሰበሰብበት ቦታ ነው፡፡ተቆጥረኽ ከዚህ ቦታ መኪና ላይ ተጭነህ ፍርድቤት ትሄዳለህ ስትመለስም ከዚሁ ቦታ ተቆጥረኽ ትገባለህ ፡፡በዚህ ለአይን በሚያደክም ግቢ ውስጥ ት/ቤቶች ፤ትንሽ ክሊኒክ፤የምግብ ማብሰያ ቤቶች ፤ ወርክ ሾፖች አሉ፡፡ከመኪናው እንደወረድክ እቃህን አሲዘው አሰልፈው በየተራ በስተቀኝ ካለ
ቢሮአቸው /ቆርቆሮ በቆርቆሮ/ ውስጥ ትገባለህ አንድ ከማርጀት አልፈው የሻገቱ ሰውዬ ከውስጥ ይጠብቁሀል እንደቆምክ
ስምህን ይጠይቁሀል ለመፃፍ ስለሚቸግራቸው ስምህን ደጋግመህ መናገር ግድ ነው፡፡ ታጋይ ስለሆኑ መሰለኝ ጡረታ
ያልወጡት፡፡ በተለይ ለመፃፍ አስቸጋሪ ስም ካለህ ትሰደባለህ ከዛም በድሮ ካሜራ የእውነት ይሁን የውሸት አላቅም ፎቶ
ያነሱሀል፡፡እዚህ ቢሮ ውስጥ የመጨረሻው ነገር ሎሚ የሚያክል መዳኒት መዋጥ ነው፡፡ እንዳትኮረሽም ይሉሀል ያን ትልቅ
መድሀኒት መዋጥ ግደታ ነው፡፡ባረጀ ጣሳ ውሀ ያቀብሉሀል እየዘገነነህ መዳኒቱ ከጉሮሮህ እንዲወርድለህ ስትል በዛ አስቀያሚ
ጣሳ ውሀውን ትጠጣለህ፡፡ በፖሊሶች እየተመራህ ወደ ዞን ሶስት ትሄዳለህ ፡፡ ይህ ዞን ማንኛውም እስረኛ ቃሊቲ ሲወርድ
በመጀመርያ ያርፍበታል፡፡እዚህ ካላረፈ ግን አንድ ነገር አለ ማለት ነው ፡፡ምን አልከኝ ምን መሰለህ ከመንግስት ጋር ንክኪ
ኖሮታል ለብቻው መታሰር አለበት አለበለዚያም ሚድያ ያናፈሰው እና ህዝብ የሚያወቀው ከሆነ ለብቻው ይታሰራል ከነዚህ
ውጪ ግን ገንዘብ ያላቸው ሰዎችና ዞን ሶስትን ጠንቅቀው የሚያቁ ሰዎች ለመዳቢው ፖሊስ ጠጋ ብሎ በጆሮው አንድ ነገር
ይነግረዋል ፡፡አንተ ጠጋ ብለህ በጆሮው ያልነገርከውን ምስኪኑን እየነዳ ካሉት ሰባት ዞኖች መሀል ዞን ሶስት ይከትሀል፡፡
ካለነሱ ፍቃድ ሌለውን ዞን ምን እንደሚመስል አታይም፡፡ማየትም የተከለከለ ነው፡፡ግራውንድ ስርም የሚታሰሩ አደገኛ
እስረኞች አሉ፡፡
ዞን ሶስት /ግቢ ሶስት/
በዚህ ዞን ውስጥ አምስት ትልልቅ ቤቶች ይገኛሉ አንድ ቁጥር ቤት፤ሁለት ቁጥር ፤ሶስት ቁጥር፤አራት ቁጥር፤ አምስት ቁጥር
፡፡ የተሰሩት ቆርቆሮ በቆርቆሮ ሲሆኑ አንደኛው ቤት ካንደኛው በቆርቆሮ ግድግዳ ይያያዛሉ ፡፡ አዲስ እስረኛ ቀጥታ አንደኛ
ክፍል ይገባል ወደሌላ ክፍል ወይም ዞን የምትዘዋወረው ከአንድ ሳምንት በኃላ ነው ፡፡ይህ ቁጥር አንድ ክፍል ከሌሎቹ
ክፍሎች ጠባብ ነው ለራስህ ካልሳሳህ እዚህ ክፍል ውስጥ ላለመኖር እራስህን ታጠፋለህ ፡፡በዞን ሶስት የሚገኙ ሌሎች
ክፍሎች እያንዳንዱ ክፍል ስፋት /40 በ 20/ ያክል ሲሆን እነዚህ ቤቶች ሻወር እና ሽንት ቤታቸው ከቤት ውስጥ ነው
የሚገኘው ፡፡በያንዳንዱ ክፍል ውስጥ ከ 200-350 እስረኛ ይኖርባቸዋል ደልቶህ እንደማትኖር እርግጠኛ ነኝ፡፡ጥቂት
ተደራራቢ አልጋዎች በየክፍሉ ሲኖሩ መሬት ላይ የሚተኙት ይበልጣሉ፡፡ገንዘብ ካለ ችግር የለውም አንድ አልጋ እስከ
1000ብር ልትገዛ ትችላለህ፡፡የምትገዛው አልጋ በወረፋ ከደረሰው ሰው ነው፡፡በድብቅ ይሰራል ቢባልም አንዳንድ ፖሊሶች
ተሳታፊ መሆናቸውን ታያለህ፡፡ይሄን ያህል ብር የሌለው እስረኛ ደቦቃ መተኛት ይጠበቅበታል፡፡
ደቦቃ ማለት ቦታ ለማብቃቃት የሚተኛ መኝታ ሲሆን የአንዱ እግር ሌላው ፊት ላይ ያደርገዋል የዛኛው ሰው እግር
እዚህኛው ፊት ላይ ይሆናል አስቀያሚ መኝታ የማትገላበጥበትና ለሽንትህ የማትነሳበት ለሊትን ትጋፈጣለህ፡፡ቆርቆሮ
በቆርቆሮው የሆነው ቤት ይግላል ያዣል፡፡አልጋ ላይ ያለው ቁልቁል ወደታች ይሄን ትይንት እያየ ያዝናል፡፡ ፍራሽ ወደ
ቃሊቲ ስትወርድ ይዘህ ካሌድክ ባዶ መሬት ላይ ትተኛለህ፡፡ቃሊቲ እንደገባህ ኪኒን እንጂ ፍራሽና ብርድልብስ አይሰጥህም፡፡
እዚህ ዞን ውስጥ አንድ ትንሽ ካፌ ፤ሁለት ፀጉር ቤቶች፤አንድ ህግ ማማከርያ ቢሮ፤በጣም ትንሽ ላይብረሪ ገፅ ከሌላቸው
መፅሀፍት ጋር፤ሶስት ከረንቡላዎች፤በጣም ትንሽ የኦርቶዶክስ ቤ/ክርስትያን በጣም ትንሽ ባዶ መሬት ኳስም እጅ ኳስም
የሚጫወቱበት ቦታ ፤የእንጨት ስራ የሚሰሩበት ትንሽ ቤት፤ በጣም የሚያስቅ ጉሊት፤ ሲጋራና ሀሺሽ በድብቅ የሚሸጡ
ሰዎች፤ እብዶች፤ሊያብዱ የተዘጋቹ ሰዎች፤አዋቂዎች ፤ ኢ-አዋቂዎች ብቻ የሰው አይነት ይገኛል ፡፡ሁሉም ዞን ላይ ይሄ
እንደሚኖር ገምት፡፡
ኮሚቴዎች ከስረኞች ይመለመላሉ በየክፍሉም አሉ
የምግብ ኮሚቴ /ምግብ ከተሰራበት ቦታ አምጥተው የሚያድሉ /
የጤና ኮሚቴ /የተማመሙትን መዝግበው ነጭ ጋዎን ለሚያደርጉ ሀኪም ተብዬዎች የሚወስዱ/ የፅዳት ኮሚቴ /የቤቱን ፅዳትን በተመለከተ የሚቆጣጠር ሲሆን ሁሉም እስረኛ በየወሩ አንድ አንድ ብር ያዋጣና የቤቱንውበት ለመጠበቅኦሞ ሳሙና ሌሎች ነገሮችንም ይገዛሉ /
የመኝታ ኮሚቴ /እስረኛው እንዲተኛ ቦታ የሚሰጡ ባይተኛም ለቂጡ ቦታ እንዲያገኝ የሚያረጉ/
የስፖርትና መዝኛኛ ኮሚቴ /በቤት ውስጥ ያለውን ቴሌብዥን እንደየቤቱ ስፋት ይለያያል አንዳንዱ ቤት ሁከት ተቪ ሊኖር
ይችላል ይሄን ተቪ የሚቆጣጠሩ የሚከፍቱ የሚዘጉ ናቸው ለሊቱን ሙሉ ፊልም ይታያል/
ሶስት የቤቱ አስተዳደሮች /ጠቅላላ የቤቱን ሁኔታዎች የሚቆጣጠሩ ሲሆኑ እንደገባህ ማስጠንቀቅያ ይሰጡሀል ከዛም ፎቶህየሌለው መታወቅያ ይሰጡሀል / በጥቂቱ ኮሚቴዎች እነዚህ ናቸው
ይቀጥላል
Ethiopia is a federal republic. On August 20, Prime Minister Meles Zenawi died. The ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) elected then deputy prime minister Hailemariam Desalegn to take Meles’s place as chairman of the party. The EPRDF subsequently nominated him for the post of prime minister. On September 21, parliament elected Hailemariam as prime minister. In national parliamentary elections in 2010, the EPRDF and affiliated parties won 545 of 547 seats to remain in power for a fourth consecutive five-year term. Although the relatively few international officials allowed to observe the elections concluded technical aspects of the vote were handled competently, some also noted that an environment conducive to free and fair elections was not in place prior to the election.
Security forces generally reported to civilian authorities; however, there were instances in which special police and local militias acted independently of civilian control.
The most significant human rights problems included restrictions on freedom of expression and association through politically motivated trials and convictions of opposition political figures, activists, journalists, and bloggers, as well as increased restrictions on print media. In July security forces used force against and arrested Muslims who protested against alleged government interference in religious affairs. The government continued restrictions on civil society and nongovernmental organization (NGO) activities imposed by the Charities and Societies Proclamation (CSO).
Other human rights problems included arbitrary killings; allegations of torture, beating, abuse, and mistreatment of detainees by security forces; reports of harsh and at times life-threatening prison conditions; arbitrary arrest and detention; detention without charge and lengthy pretrial detention; a weak, overburdened judiciary subject to political influence; infringement on citizens’ privacy rights, including illegal searches; allegations of abuses in the implementation of the government’s “villagization” program; restrictions on academic freedom; restrictions on freedom of assembly, association, and movement; alleged interference in religious affairs; limits on citizens’ ability to change their government; police, administrative, and judicial corruption; violence and societal discrimination against women and abuse of children; female genital mutilation/cutting (FGM/C); exploitation of children for economic and sexual purposes; trafficking in persons; societal discrimination against persons with disabilities; clashes between ethnic minorities; discrimination against persons based on their sexual orientation and against persons with HIV/AIDS; limits on worker rights; forced labor; and child labor, including forced child labor.
Impunity was a problem. The government, with some reported exceptions, generally did not take steps to prosecute or otherwise punish officials who committed abuses other than corruption.
Factions of the Ogaden National Liberation Front (ONLF), an ethnically based, violent, and fragmented separatist group operating in the Somali Region, were responsible for abuses. Members of the separatist Afar Revolutionary Democratic Union Front (ARDUF) claimed responsibility for a January attack on a group of foreign tourists in the Afar Region.