Tuesday, March 10, 2015

Ethiopia: Digital Attacks Intensify (Human Rights Watch)

March 9, 2015
(New York) – The Ethiopian government has renewed efforts to silence independent voices abroad by using apparent foreign spyware, Human Rights Watch said today. The Ethiopian authorities should immediately cease digital attacks on journalists, while foreign surveillance technology sellers should investigate alleged abuses linked to their products.
Ethiopia: Stop Using Anti-Terror Law to Stifle Peaceful Dissent
Independent researchers at the Toronto-based research center Citizen Lab on March 9, 2015, reported new attempts by Ethiopia to hack into computers and accounts of Ethiopian Satellite Television (ESAT) employees based in the United States. The attacks bear similarities to earlier attempts to target Ethiopian journalists outside Ethiopia dating back to December 2013. ESAT is an independent, diaspora-run television and radio station.
“Ethiopia’s government has over the past year intensified its assault on media freedom by systematically trying to silence journalists,” said Cynthia Wong, senior Internet researcher at Human Rights Watch. “These digital attacks threaten journalists’ ability to protect the safety of their sources and to avoid retaliation.”
The government has repressed independent media in Ethiopia ahead of the general elections scheduled for May, Human Rights Watch said. Many privately owned print publications heavily self-censor coverage of politically sensitive issues or have shut down. In the last year, at least 22 journalists, bloggers, and publishers have been criminally charged, at least six publications have closed amid a campaign of harassment, and many journalists have fled the country.

Monday, March 9, 2015

ምርጫውን ለህዝባዊ እንቢተኛነት እንዴት?

ዳዊት ዳባ
ህዘባዊ እንቢታ ማለት ዜጎች የስርአት ለውጥን ሆነ መብታቸውን ለማስከበር በብዙ ቁጥር ሆነው በጋራ አንድን ነገር ማደረግ ወይ አለማድረግ ነው። አለቀ። ብብዙ ቁጥር ተቃውሞ አደባባይ መውጣት በጋራ ልናደርጋቸው ከምንችላቸው በትንሹ ከሺ ነገሮች ውስጥ አንዱ የህዝባዊ ተቃውሞ አካል ነው። ተቃውሟችንን ለመግለፅ በጋራ ልናደርጋቸው የሚቻሉን ነገሮች ሁሌ የግድ ከባድም አጋላጭም መሆንም የለባቸውም። በይበልጥም ስንጀምረው።
Statement from 9 Ethiopian coalition parties
ማወቅ ያለብን አምላክ የሰውን ልጅ ሲፈጥር እስከነፃነቱ እንዲሆን አልሞ ነው። ሲፈጥረው ባስፈለገው ጊዜ አፈጣጠሩን በሙሉ ነፃነቱን ማስጠበቂያ አድርጎ እንዲጠቀምበት ነው። ሀሰት የሚል ካለ ይህንን አፈጣጠሩን ነፃነቱንና መብቱን ማስከበርያ አድርጎ ሊጠቀምበት አይችልም ይበል። እኛም ኢትዬጵያዊያን ሰዎች ነን። የሰው ልጅ እንደመሆናችን ስሜታችንን ፤ አካላዊ እንቅስቅሴያችንን፤ ውስጣዊም ሆነ ውጫዊ አካላችንን ፤ድርጊታችንን፤ አኗኗራችንን፤ የማሰብ ችሎታችንን፤ ፍላጎችንን፤ድምፃችንን ብቻ ሁለንተናዊ አፈጣጠራችንን መጠቀሙን እናውቅበታለን አናውቅበትም ነው እንጂ ጉልበታሞችን ልክ ማስገቢያ ካምላክ የተሰጠ ሀይላችን ነው።
ነፃነቱን ገፋፊው አንድ ግለሰብ ሲሆን ተገፋፊው ይሰራል ያለውን አፈጣጠሩን ተጠቅሞ በመዝጋትም ሆነ ልክልኩን በመንገር እንደሁኔታው አናቱን በድንጋይ በመበርቀስ ነፃነቱንና ክብሩን ማስመለስ ይችላል። ነፃነቱን የቀማው መንግስት ሲሆን ግን ብቻውን ሆኖ አደባባይ ላይ ወጥቶ በመጮህ ሆነ ተኩሶ እንዳሰበው ተፅኖ ፈጣሪና ውጤታማ ትግል ለማካሄድ ሁሌ የተሳካ ላይሆን ይችላል። በወረደ ምሳሌ፤- አንድ ሰው ብቻውን አገዛዝን ለመታገያና ተቃውሞውን ለመግለፅ አስቦ እደጅ ቢፀዳዳስ። ሲጀመር እስከጭራሹ ለምን እንዳደረገውም ላይታወቅ ሁሉ ይችላል። ነግር ግን ነፃነታቸውን የተነፈጉ በሙሉ አንድ ቀን ወስነው እጅ ለእጅ ተያይዘው እደጅ ቢፀዳዱስ። ይህ በቀጥታ ነቅንቅ የሆነ ተቃውሞ መሆኑ ጥያቄ ውስጥ አይገባም። { አይዞን ምሳሌ ነው። ካስፈለገ ተባብሮ ማፅዳቱንም ቀጣይ የተቃውሞ አይነት ልናደርገውም እንችላለን }።

Tuesday, March 3, 2015

ክፉን ሰውና ክፋተኝነትን እንዴት እናውቃለን?

በ ይሄይስ አእምሮ
Pen
ርዕሴ በጣም እንዳይጮኽብኝ ፈርቼ እንጂ ላደርገው አስቤና ፈልጌም የነበረው “ሰይጣንና ሰይጣናዊነት እንዴት ይታወቃሉ?” የሚል ነበር፡፡ ይህ ጽሑፌ በዚሁ ተመሳሳይ ጉዳይ ዙሪያ ባለፈው ሰሞን በአንዳንድ ድረ ገፆች የወጣውን በሴቴኒስቶች የሰላምታ መለዋወጫ ምልክቶች ምስል የተደገፈ አነስተኛ መጣጥፍ የተከተለ  ነው፡፡ ከሁሉ በፊት ግን ቀጣዩን ሥነ ቃላዊ ትውፊት ለነገሬ መነሻነት ባስቀድም ደስ ይለኛል፡፡

የቸገረው ሰው ከገባበት የችግር ማጥ ለመውጣት የማያደርገው ነገር የለም፡፡ አንዲት ሴት፣ ልጅ መውለድ እምቢ ይላትና ለዐርባ አራቱም ታቦት ትሳላለች፤ በዚያም አልሆነላትም፡፡ በየጠንቋዩና በየደብተራው ቤትም ደጅ ትጠናለች፤ በዚያም አልሆነም፡፡ በየጠበሉና በየሀኪም ቤቱም ትንከራተታለች፤ አሁንም በዚያም አይሆን ይላታል፡፡ ቢጨንቃት ለሰይጣን ትሳላለች፡፡ ስለቷም “አንተ እንደኔው የእግዜር ፍጡር የሆንክ ሰይጣን ሆይ! ልጅ እወልድ ብዬ ብዙ ተሳልሁ፤ ወጣሁ ወረድሁ ግን አልሆነልኝም፡፡ አሁን ደግሞ ባንተ በኩል ልሞክር ወስኛለሁ፡፡ ስለዚህ እስከዛሬ ዓመት ድረስ ወንድ ልጅ ከነቃጭሉ ከሰጠኸኝ ራሴው ፈትዬ አንድ ቡልኮ በስለት አስገባልሃለሁ” የሚል ነው፡፡
የአጋጣሚ ነገር ሆነና ልክ ባመቱ የሰማ ሰምቷት አንድ ወንድ ልጅ ከነቅጭልጭሉ ትወልዳለች፡፡ ደስታዋም ከጣሪያ በላይ ይሆናል፡፡ ከአራስ ቤት ጀምራ ትፈትልና በክርስትናው ማግሥት ለሰይጣን የተሳለችውን ቡልኮ በዕውቅ ሸማኔ አሠርታ ዝግጁ ታደርጋለች፡፡ ነገር ግን ያላሰበችው ችግር ይገጥማታል፡፡ ሰይጣንን የት አግኝታ ትስጠው? ችግር እኮ ነው፤ አንዱ ሲሟላ አንዱ አይሟላም፡፡
በየመንደሩና በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን እየዞረች “የሰይጣንን ቤተ ‹ክርስቲያን› ያያችሁ ነይ ወዲህ በሉኝ” ብትል ማን ዐውቆት ያሳያት? ብዙ ትለፋለች፤ ትደክማለችም፤ ነገር ግን በክንዷ አንጠልጥላ የምትዞረውን ቡልኮ ወይም ጋቢ የሚረከባት አንድም ሰይጣን ይጠፋል፡፡
ችግሯን ያስረዳቻቸውና የገባቸው አንድ ብልህ ሽማግሌ ግን እንዲህ ሲሉ ይመክሯታል፡፡ “አንቺ ሴትዮ፣ ልጅ ለመውለድ ያደረግሽው ጥረት በውነቱ የሚገርምና ታይቶም ሆነ ተሰምቶ የማያውቅ ነው፡፡ አሁን ሰይጣንን ካላገኘሽውና ቤቱንም ካጣሽው በአማራጭነት እንዲህ አድርጊ፡- እሁድ ቀን ወደ አንዱ ቤተ ክርስቲያን ሂጂ፡፡ ከዚያም ማርገጃው አካባቢ ሽማግሌዎች ተሰብስበው የተጣሉ ወይም የተቀያየሙ ሰዎችን በሚያስታርቁ ጊዜ የሽማግሌ ቃል አልሰማም ብሎ ንቋቸው ከጉባኤው እመር ብሎ የሚወጣ ሰው ስታገኚ ‹በስምህ የተሳልሁትን ልሰጥህ ስፈልግህ ኖሬ ዛሬ ገና አገኘሁህ፤ ይሄውልህ ቡልኮህ› በይና ትከሻው ላይ ጣይለት፤ ሰይጣን ማለት ዕርቅና ሰላምን የማይወድና የማይፈልግ ነውና እዚያ ማርገጃው ላይ በሰው ተመስሎ ታገኝዋለሽ፡፡” ይላታል፡፡
‹ሞኝ የነገሩትን፤ ብልህ የመከሩትን› ነውና ያቺ ሴት እንደተባለችው ቤተ ክርስቲያን እየሄደች ያን መሳይ ሰው ታጠምድ ያዘች፡፡ አንድ ቀንም እንደድንገት ሃሳቧ የሚሣካበት ምቹ አጋጣሚ ይፈጠራል፡፡ አንድ ደመ ሞቃት ሰው የሽማግሌዎችን ምክርና ተግሣጽ እንዲሁም የማስታረቂያ ሃሳብ ንቆ “ደግሞ እናንተን ብሎ አስታራቂ! ቀልማዳ ሁላ፤ እኔ ነኝ ደግሞ ‹በድየሃለሁና ይቅር በለኝ ብዬ እሱ እግር ላይ የምወድቅ?› የወሬ ቋቶች! …” በማለት ተስፈንጥሮ ከጉባኤው ሲወጣ ታየዋለች፡፡ ይሄኔ በደስታ እየተፍነከነከች አፈንጋጭ ጎልማሣውን ጠጋ ትልና “እሰይ! እንኳን አገኘሁህ! አሁን ገና ገበያየ ሞላ! ለስንት ጊዜ ስፈልግህ ኖሬ ዛሬ ገና ተሳካልኝ፡፡ በል ስለትህን ተረከበኝ” ትልና ቡልኮውን እሰውዬው ትከሻ ላይ ትጥልለታለች፡፡