እንደ ኢትዮጵያ ከልመናና ከምጽዋት ጋር ስሙ የሚነሳ ብዙ አገር የለም። ላለፉት ሰላሳና አርባ አመታት የቆየ ሀቅ ነው። በችጋር ጊዜ መለመን ግድ ሊሆን ይችላል። ሁሌ መለመን ግን ህመም ነው። እኛ ግን ከልመና ጋር ከመለማመዳችን የተነሳ ይመስላል ፈጽሞ ሲረብሸን አይታይም። እንዲያውም የተመቸን ነው የሚመስለው። ፖለቲካችን ሁሉ ልመና ተኮር ነው። የአገሪቱ ዲፕሎማቶች ዋነኛ ስራቸው ተግቶ መለመን ሲሆን ሲሳካላቸው ‘በተደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ይህን ያህል ርዳታ ተገኘ’ ብለው በሚቆጣጠሩት ቲቪ ያውጃሉ። እንደ ድል ብስራት እኮ ነው የሚያዩት። አንዳንድ ተቃዋሚዎቻቸው ደግሞ ርዳታ እንዳይገኝ ማሰናከል (ማቃጠር በሉት) ላይ ተጠምደዋል። ሃያላን መንግስታትና እነሱው የሚቆጣጠሯቸው እንደ አለም ባንክ ያሉ ድርጅቶች ርዳታ እንዳይሰጡ መወትወት። እንዴት ያሳፍራል። ሁለቱም አቅመቢስነትን ከመቀበል ይመነጫሉ፤ እኛ ምንም ለማድረግ አቅም የለንምና ይሄን ስጡኝ ወይ ደግሞ ያን አትስጡብን እኮ ነው ነገሩ። ስለራስ አቅም ሳይሆን በሌላ ሰው ወይም አካል ቁጥጥር ስር ያለን ሀብት/አቅም አንጋጦ የማየት በሽታ ነው። ልመናውም ምጽዋት ማከላነሉም (ምቀኝነቱ) የጥገኝነት አባዜን ከማንጸባረቅ ባለፈ ግን አንድም ነገር አይለውጥም። የሞራል ጥያቄውን ብንተወው እንኳን በአለም ታሪክ በልመና ታሪክ የሰራ አገር የለም፤ ቢኖር ኖሮ ማን ይቀድመን ነበር? በአንጻሩ ምጽዋት ጠባቂነት አንድን ህዝብ ከልመና ለመውጣት ከሚያዳግትበት አዙሪት ውስጥ ሊቀረቅረው ይችላል። እዚያ አዙሪት ውስጥ አይደለንም ብሎ መናገር የሚቻል አይመስለኝም። ይህን አዙሪት ለመረዳት ሀብታሞች ለምን እንደሚረጥቡን መጠየቅ ያስፈልጋል።
Monday, May 11, 2015
Monday, May 4, 2015
Anti-Police Protest in Israel Turns Violent
TEL AVIV — A protest on Sunday by thousands of Ethiopian-Israelis and sympathizers against police harassment and brutality turned by nightfall into a chaotic and unusually violent confrontation with the police in the center of Tel Aviv.
The demonstration began peacefully in the afternoon with protesters blocking main thoroughfares of Tel Aviv, paralyzing the heart of the city for hours as officers looked on and stopped the traffic. Later, demonstrators hurled stones, overturned a police vehicle and clashed with the police in Rabin Square. Officers responded with stun grenades and water cannons.
About 46 people were slightly injured, half of them police officers, and at least 26 protesters had been arrested by midnight, according to the police.
Prime Minister Benjamin Netanyahu called for calm, saying, “All claims will be looked into but there is no place for violence and such disturbances.”
The police said that agitators had stirred up the atmosphere. Many here compared the cry of the young, angry generation of Ethiopian-Israelis who came out on Sunday to the tensions in American cities like Baltimore or Ferguson, Mo., that have been roiled by friction between blacks and the police.
Friday, May 1, 2015
አሜሪካ አይሲስን ለምን ፈጠረችው?
(ክንፉ አሰፋ)
ግብጽ የሃያ አንድ ክርስቲያን ዜጎችዋን በአይሲስ መታረድ ዜና እንደሰማች ዝም ብላ አልተቀመጠችም ነበር። ብሄራዊ የሃዘን ቀንም አላወጀችም። እንዲህ ነበር የሆነው። ከመቅጽበት ተዋጊ አውሮፕላኖችዋን አስነስታ ወደ ሊቢያ ላከቻቸው። የአይሲስ አራጆች የተከማቹበትን ደርና የተሰኘ ስፍራ እያከታተለች በቦምብ ቀጠቀጠችው። ብዙ አራጆች በድብደባው አለቁ። እንደ ግብጽ አጀማመር ቢሆን የሊብያው አይሲስ ክንፍ ድሮ-ድሮ ከምድረ-ገጽ ይጠፋ ነበር። ግና አልሆነም። አሜሪካ ጣልቃ ገባች። ግብጽ የአሜሪካን “ጸረ-ሽብር” ዘመቻ በማገዝዋ ምስጋና ማግኘት ሲገባት በተቃራኒው ተወገዘች። ከጥቂት ድብደባ በኋላ ፔንታጎን ግብጽን አስጠነቀቀ[0]። የኦባማ አተዳደርም ደብደባው በአፋጣኝ እንዲቆም ቀጭን መልእክት ላከ። ይህ ድርጊት ከዚህ ቀደም ስለ አይሲስ አፈጣጠር ኤድዋርድ ስኖደን[1] የለቀቀው ምስጢራዊ መረጃ ጋር ተዳምሮ በአሜሪካ ላይ የነበረውን ጥርጣሬው አጠናከረው።
ነገሩን ለማመን ያዳግት ይሆናል። በግልጽ የሚታዩ መረጃ እና ማስረጃዎች ግን ተአማኒነታቸው ጥርጥር ውስጥ የሚገባ አይደለም። “በአይሲስ እየታረዱ ያሉት ዜጎች የፊልም ቅንበር እንጂ እውነት አይደለም![2]” የሚሉ ባለሞያዎችም የትንተናቸው መነሻ ከዚህ ጉዳይ ጋር ይያያዛል።
ይህ አሸባሪ ድርጅት ስራውን ከጀመረ አንድ አመት ባልሞላ ግዜ ውስጥ ከመቶ ሺ በላይ ዜጎችን በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደለ ይናገራል። ቦምብ እንደዝናብ የሚወርድባቸው ሃገሮች፤ ሶማልያ፣ የመን፣ ኢራቅ፣ ሶርያ፣ አፍጋኒስታን፣ፓኪስታን… ተደምረው አይሲስ ከሚነግረን ግድያ ሩብ ያህሉንም አላደረጉም። የሃያላን ሃገሮች ምላሽ ግን በአፍ ከማውገዝ ያለፈ አለመሆኑ በአይሲስ አሰራር ላይ ተጨማሪ ጥርጣሬ ይፈጥራል።
Subscribe to:
Posts (Atom)