Friday, November 7, 2014

የአንድነት ፓርቲ እንዲዳከም ወይም ከምርጫው ዉጭ እንዲወጣ በአገዛዙ እየሰራ ነው

እሥሩ ተጧጡፏል፣ አንድነት ምርጫ እንዳይወዳደር አገዛዙ ይፈልጋል (ግርማ ካሳ)

ዜጎች መታሰራቸው እየቀጠለ ነው። በተለይም የአንድነት ፓርቲ አባላት (በጎንደር፣ በትግራይ፣ በመቱ፣ በአዲስ አበባ ፣ በወላይታ ….) ። ብዙዎች ከፍተኛ ደብደባ እየደረሰባቸው ነው። ሕወሃት ፣ በሕዝብ እንደተጠላ ስላወቀ የአንድነት ፓርቲ እንዲዳከም ወይም ከምርጫው ዉጭ እንዲወጣ እየሰራ ነው። አንድነት ሊያሸንፈው እንደሚችል ስላወቀ።

የድርጅቶች መተባበር አስፈላጊ በመሆኑ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር ተስማምቶ የቅድመ ዉህደት ስምምነት ፈርሞ ነበር። ሁሉም ነገር አልቆ ነበር። ሆኖም ምርጫ ቦርድ ወይንም አገዝዙ፣ ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ ዉህደቱን አስቁሞታል። ይኸው እስከአሁን ድረስ በአቶ አበባው ለሚመራው መኢአድ እውቅና አልሰጠም ብሎ መኢአዶችን ምርጫ ቦርድ እያጉላላቸው ነው።

የአንድነት ፓርቲ በቅርቡ በድርጅቱ ሕገ ደንብ መሰረት፣ አዲስ አመራር መርጦ መንቀሳቀስ መጀመሩም ይታወቃል። ሆኖ ምርጫ ቦርድ/ ሕወሃት ፣ በንድነት ዉስጥ አስርጎ አስገብቷቸው ከነበሩን በአንድነት እንዲራገፉ ከተደረጉት 2፣ 3 ግለሰቦች ጋር በመመካከር፣ እንደገና ለአዲሱ የአንድነት አመራር እውቅና አልሰጠም እያለ ነው። (የዛሬዉን ሰንደቅ ያንብቡ) ምናልባትም መኢአድ እና አንድነት ከምርጫዉ ሊያግዳቸው፣ አሊያም የነርሱን ሰርተፊኬት፣ ቅንጅትን ለአየለ ጫሚሶ እንደሰጠው፣ ለነ ማሙሸትና እና ለነ ዘለቀ ረዲ ሊሰጣቸውም ይችልም ይሆናል።

አገዛዙ እያሰረ፣ ድርጅቶችን እያገደ፣ ሽብርተኞች እያለ ፣ አይኑን በጨው አጥቦ የፊታችን 2007 ምርጫ አሸነፍኩ ማለቱ አይቀርም። የዉጭው አለም ምንም አይለም። (99.9 በመቶ ሲያሸንፉም የዉጭ አለም ያደረገው ነገር የለም) ። ሆኖም ሕዝቡ ግን ወደ አመጽ መሄዱ አይቀሬ ነው። ሕዝቡ ቀንበር በዝቶበታል። ያሉት መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ የኑሮ ዉድነቱ፣ ዘረኝነቱ፣ የባለስልጣናት ጥጋብ ብዙዎችን በጣም እያማረረ ነው። ፖለቲካው በጣም እየከረረ ነው። እነዚህ ሰዎች ተመረጥን ብለው ቢያወጁም ፣ ያለ ምንም ጥርጥር በሕዝባዊ አመጽ መዉደቃቸው አይቀርም። በዚህ ሁኔታ ሕዝቡን ሊገዙ አይችሉም።

የምመርጠው በሰላማዊ ምርጫ ሕዝቡ ፍላጎቱን እንዲያንጸባርቅ ነው። ሕዝቡም ገዢዎችን ተጠያቂ የሚያደርገው በምርጫ ቢሆን ጥሩ ነው ያንን የምርጫ አማራጭ ገዢዎች ከወሰዱበት ህዝቡ ሌላ መንገድ መፈለጉ አይቀርም።

ለዚህ ነው ገዢዎች ልብ እንዲገዙ አሁንም የምመከረው። ምርጫው ፍትሃዊና ነጻ እንዲሆን ማድረግ አለባቸው። «በምርጫ 2007 ጥሩ ነገር አይተናል፣ ከዚያ በኋላ ያለዉን ደግሞ በ2012 ደግሞ እናስተካክለዋለን » የሚል ሐሳብ ዜጎች እንዲኖራቸው ማድረግ አለባቸው። አለበለዚያ 2012 የሚጠብቅ አይኖርም። ዜጎች አገዛዙን እንደ ግራዚያኒ አገዛዝ ቆጥረው ፣ አገዛዙን ለማስወገድ መንቀሳቀስ ይጀምራሉ።UDJ-SEAL

Wednesday, November 5, 2014

Human rights campaigner says African Union should move headquarters out of Ethiopia

November 5, 2014
by: CHRISTOPHER TORCHIA , Associated Pres
JOHANNESBURG — The African Union should move its headquarters out of Ethiopia because of concerns about freedom of expression there, an Angolan journalist and human rights campaigner said.
african union headquarters
Journalist Rafael Marques de Morais, who has been jailed and faces numerous legal challenges for his investigative work in Angola, said in Johannesburg on Tuesday night that the African Union is hypocritical for keeping its base in Addis Ababa, the Ethiopian capital. The union represents 53 countries on the continent and says it is committed to transparency and human rights.
Marques cited the ongoing Ethiopian trial on terrorism-related charges of bloggers from Zone 9, a collective that publishes critical news and commentary. He also mentioned the three-year prison sentence handed last week to Temesgen Desalegn, the former editor of the now-defunct newspaper Feteh who was convicted of charges including incitement.

Tuesday, November 4, 2014

የተረገዘው እንዲወለድ



የኢትዮጵያ ህዝብ ለውጥ ይፈልጋል አይፈልግም የሚለው ጥያቄ አከራካሪ አይመስለኝም። ፌስ ቡክ ተጠቃሚውን ብቻ አይቶ የህዝቡን ፍላጎት መረዳት ይቻላል። ተመራማሪዎች በአንድ አገር ያለውን የህዝብ ስሜት ለማወቅ እስከ 2 ሺ የሚደርሱ ሰዎችን አነጋግረው ድምዳሜ ላይ ይደርሳሉ። እኔም ካሉኝ 5 ሺ የፌስቡክ ጓደኞች መካከል ፣ ፖለቲካን ከሚከታሉት ውስጥ ማለቴ ነው፣ ከ90 በመቶ በላይ ለውጥ ፈላጊዎች ናቸው። ሁሉም ፌስቡከር ተመሳሳይ ናሙና ወስዶ ጥናት ሊያካሂድ ይችላል። እጅግ የሚበዛው ህዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ለውጡ በምን መንገድ ይሁን- በአብዮት ወይስ በዘገምተኛ ለውጥ፣ በትጥቅ ትግል ወይስ በሰላማዊ ትግል- ሰላማዊ ትግል ሲባልስ- በህዝባዊ አመጽ ወይስ በየ5 አመቱ በሚደረግ ምርጫ በሚለው ላይ የአሃዝ ልዩነት ሊኖር ይችላል። ስርዓቱ እንዲለወጥ በመፈለግ በኩል ግን ካላጋነንኩ 5 በመቶ ከሚሆኑት ባለስልጣኖችና ተጠቃሚዎች በስተቀር እጅግ አብዛኛው ህዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ባለፉት 4 ዓመታት ካነጋገርኳቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ተነስቼ ከማንም በላይ በቅድሚያ ለውጥ ፈላጊው በመካከለኛ ደረጃ ያለውና ተራው ወታደር መሆኑን መመስከር እችላለሁ። ስሜቱን የሚገልጽበት መድረክ ስላላገኘ እንጅ ወታደሩ ትንሽ ነገር የሚጠብቅ ፣ በቋፍ ላይ ያለ፣ ለለውጥ ዝግጁ የሆነ ሃይል ነው።

አብዛኛው ህዝብ ለውጥ ፈላጊ እስከሆነ ድረስ ለውጥ አይቀርም። ጭቆናም እስካለ ድረስ አመጽ አይቀሬ ነው ። በኢትዮጵያ የሚመጣው የስርዓት ለውጥ ህዝባዊ አመጽና ሃይልን ያማከለ ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ። የሃይል አማራጩ እየተጠናከረ ሲመጣ፣ የሲቪሉም የለውጥ እንቅስቃሴ እየጎለበተ ይመጣል፣ ወይም በተቃራኒው። ብዙዎች ሁለቱን ሃይሎች ተጻራሪ አድርገው ይመለከቷቸዋል። የሃይል አማራጭ መኖር ህዝባዊ አመጽን ወይም ሰላማዊ ትግልን ያዳክማል ብለው ይሰጋሉ። ለእኔ ደግሞ ህዝባዊ አመጽና የሃይል አማራጭ ተደጋጋፊ እንጅ ተጻራሪ ሃይሎች አይደሉም። የተቃዋሚዎች የሃይል ትግል ሲጠናከር፣ የገዢው ሃይል እየተዳከመ ይሄዳል። የገዢው ሃይል ሲዳከም ደግሞ ህዝባዊ አመጸኞች የልብ ልብ ይሰማቸውና ህዝባዊ አመጻቸውን ይቀጥላሉ። ሃይል ያላቸው ወገኖች ህዝባዊ አመጽ ለሚያካሂዱት ሽፋን ከመስጠት አልፎ፣ ድምር ሃይል ስለሚፈጥሩ የገዢውን ፓርቲ ሃይል ለመቋቋም በሂደትም ለማሸነፍ ያስችላቸዋል። የተደራጀ የሃይል አማራጭ መኖሩ በህዝባዊ አመጽ ለሚነሳ የስልጣን ክፍተት ( power-vacuum) መሙያ ይሆናል፤ የገዢው ፓርቲ ተማኝ ወታደሮች የስልጣን ክፍተቱን ተጠቅመው በአመጸኞች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ቢነሱ ወይም ለዘረፋ ቢነሱ ወይም ቢሸፍቱ ወዘተ አዲሶቹ ሃይሎች ማስታገሻ ኪኒን ይሰጧቸዋል። ህዝቡ የስልጣን ክፍተት እንደማይኖር ዋስትና ካገኘ ደግሞ ህዝባዊ አመጹን በሙሉ ልብ ለማካሄድ ያስችለዋል። የስልጣን ክፍተት ይፈጠራል ብሎ የሚሰጋ ሃይል ስለማይኖር ለውጥ ፈላጊው በአንድ ልብ ሊነሳ ይችላል።

ሁለቱ ሃይሎች ተደጋግፈው ይቀጥሉ ዘንድ አንድ ቅድመ ሁኔታ መቀመጥ አለበት ። ህዝባዊ አመጸኞችም ሆኑ የሃይል አማራጭ አቀንቃኞች፣ የሲቪል አስተዳደርና ዲሞክራሲ ለመመስረት የወሰኑና ከዚህ ውጭ ሌላ አማራጭ ለመከተል ፈቃደኞች ያልሆኑ መሆን አለባቸው። በዚህ ጉዳይ ላይ ከተስማሙ ( በሃሳብ ማለቴ ነው) ትግሉ ፈር ይዞ ይቀጥላል። ህዝባዊ አመጸኞች በህዝብ ድምጽ ለሚመጣ ስልጣን ሲታገሉ ፣ ነፍጥ ያነገቱት በተቃራኒው በመሳሪያ ለሚመጣ ስልጣን የሚታገሉ ከሆነ ፣ አንዱ የሌላው ተቀናቃኝ እንጅ ደጋፊ ወዳጅ ሊሆን አይችልም፤ ድምር ሃይል ስለማይፈጥሩም አያሸንፉም፣ ቢያሸንፉም እንኳ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ማካሄድ አይችሉም። ስለዚህም ነው፣ ዲሞክራሲን ለመገንባት ቁርባን የወሰደ ታጣቂ ሃይል ግድ የሚለው። ይህ ሃይል ከዲሞክራሲ ውጭ ሌላ አይዲዮሎጂ ወይም ሌላ የሚታገልለት አላማ ሊኖረው አይገባም። እንዲህ አይነት ግልጽ አላማ ይዞ የተነሳ ታጣቂ ሃይል ካለ ፣ ለህዝባዊ አመጽ ትግሉ ደጋፊ ሃይል እንጅ ተጻራሪ ሃይል ተደርጎ ሊወሰድ አይገባውም።
ታጣቂ ሃይሎች ከነፍጥ ባሻገር የዲሞክራሲን ዝናር መታጠቅ ግድ እንደሚላቸው ሁሉ ፣ ህዝባዊ አመጸኞችም ሊታጠቋቸው የሚገቡ ዝናሮች አሉ። ሁሉም ህዝባዊ አመጸኞች የትግሉ ዋና አላማ ስልጣን ከህዝብ ፍላጎት የሚነጭ መሆኑን አምነው መቀበል፣ ከዚህ ውጭ የሚመጣ ነገር ሁሉ ተቀባይነት የማይኖረው መሆኑን አምነው መቀበል ብቻ ሳይሆን ለተግባራዊነቱም መስራት አለባቸው። ስምምነቱንም አመጹን ከመጀመራቸው በፊት ማካሄድ አለባቸው። ህዝቡም ይህን ማድረጋቸውን ማረጋጋጥ አለበት። በዚህ ጉዳይ ላይ ከተስማሙ ገዢዎች ሊከፋፍሉዋቸው፣ በስልጣን ወይም በገንዘብ ደልለው ከዋና መስመራቸው ሊያስወጡዋቸው አይችሉም። የተረገዘው ለውጥም ቀኑን ጠብቆ ይወለዳል።

kFasil Yenealem