Ethiopian politica Views and News

Freedom,Justice,and Equality in Ethiopia

Pages

  • Home
  • Dceson
  • Ginbot7.org
  • ESAT Ameharic news

Sunday, May 24, 2015

ኢትዮጵያና አሜሪካ

(ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም)
eth and the us
May 20, 2015 08:06 am By Editor 1 Comment
ዱሮ ዱሮ ምዕራባውያን የሶቭየት ኅብረትን ኮሚዩኒዝም መስፋፋት ለመቋቋም ከእሥራኤል ሌላ አጋር ሊሆኑ የሚችሉ አገሮችን ሲያስሱ፣ ኢትዮጵያ፣ ቱርክና ፋርስ እየታጩ ነበር፤ አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የተወዳጀበትና በአስመራ ቃኘው ጣቢያን የተከለበት አንዱ ምክንያት ይኸው ነው፤ የፋርስ ጉዳይ ከንጉሠ ነገሥቱ መፈንቅለ መንግሥትና ሞት ጋር አበቃ፤ ቱርክ እያንገራገረም ቢሆን የሰሜን አትላንቲክ አገሮች ማኅበር ውስጥ አለበት፤ እሥራኤል በአረቦች አካል ላይ እሾህ እንደሆነች ጥጋበኛ የአሜሪካ ቅምጥል ሆናለች።
የፋርሱ ጉዳይ ከፋርሱ ንጉሠ ነገሥት ጋር እንደተያያዘው ሁሉ የኢትዮጵያም ጉዳይ ከኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ጋር የተያያዘ ነበር፤ የእውቀት ጥበብ (ቴክኖሎጂ) እያደገ ሲሄድ የቃኘው ጣቢያ ለአሜሪካ አማራጭ የሌለው መሆኑ ቀረ፤ አሜሪካ ኮተቱን ይዞ ወደህንድ ውቅያኖስ ሲሄድ ኢትዮጵያን ችላ ማለት ተጀመረ፤ መቃቃሩ እየበረታ ሲሄድ የአሜሪካ እብሪትና የኢትዮጵያ ኩራት ተጋጩ፤ አጼ ኃይለ ሥላሴ የአሜሪካኑን አምባሳደር አስከማስወጣት ደረሱ፤ ጨዋታ ፈረሰ ዳቦ ተቆረሰ ያኔ ተጀመረ፤ የፋርሱ ንጉሠ ነገሥት ሲገለበጥ ቀጣዩ አገዛዝ ከአሜሪካ ጋር ጠላት እንደሆነው የአጼ ኃይለ ሥላሴም አገዛዝ ሲገለበጥ ቀጣዩ አገዛዝ ከአሜሪካ ጋር ጠላት ሆነ።
አሜሪካ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያውያን ጉዳይ ጣልቃ እየገባ የፈጸመውና እየፈጸመ ያለው ግፍ የጀመረው ከዚያ ወዲህ ነው፤ የደርግ አገዛዝ ኮሚዩኒስት መሆኑን አወጀ፤ የደርግ አገዛዝ ከሶቭየት ኅብረት ጋር ማኅበርተኛ መሆኑን አወጀ፤ የደርግ አገዛዝ የአሜሪካ መንግሥት ዓለም-አቀፍ ቄሣራዊነትን የሚያራምድ መሆኑን እየደሰኮረ የአሜሪካ ባላጋራ መሆኑን አስታወቀ፤ ይህ ሁሉ እውነት ነው፤ ነገር ግን አንዱም የኢትዮጵያን ሕዝብ ፈቃድ ያዘለ አይደለም፤ አንዱም ኢትዮጵያን እንደአገር የሚያስጠይቅ አይደለም።
Read more »
Posted by Unknown at 11:48 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Friday, May 22, 2015

የወያኔን የይስሙላ ምርጫ አስመልክቶ ከዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተላለፈ ጥሪ

May 22, 2015
የተከበራችሁ እናቶቼና አባቶቼ፤ እህቶቼና ወንድሞቼ እንዲሁም ልጆቼ የምትሆኑ ወጣቶች!! አገራችን የምትገኝበትን አስጨናቂ ሁኔታ ሁላችንም እንረዳለን። የህወሓት/ኢሕአዴግ ፋሽስቶች ቡድን እየገረፈ፣ እያሰረና እየገደለ በካርዳችሁ መርጣችሁ የምርጫ ድግሴን ካላሞቃችሁልኝ እያለ ነው። እንኳንስ ዛሬ ታዛቢ በሌለበት፤ ታዛቢ እያለም እንኳን ወያኔ የሕዝብን ድምጽ በትክክል ቆጥሮ አያውቅም። ወያኔ ለህዝብ ድምጽ ምንም ደንታ የሌለው የኋላቀር ወሮበሎች ቡድን ነው::
Dr. Berhanu Nega’s election message to the Ethiopian people
ለስንት አስርት ዓመታት ለወያኔ ባርነት እንገብራለን? ለሀያ አስምስት ዓመታት ተገዛን፣ ተገደልን፣ ተቀጠቀጥን፣ ታሰርን፣ ተሰቃየን፣ ልጆቻችን በአገራቸው ተስፋ ቆርጠው ሲሰደዱ በበረሀ ንዳድ አለቁ፤ በባህር ሰጥመው ቀሩ፤ በባዕዳን አረመኔዎች እንደከብት ታረዱ፤ ቤንዚን ተርከፍክፎባቸው ተቃጠሉ። ሀይማኖታችን ተዋረደ፤ ባህላችን ረከሰ፤ ታሪካችን ተናቀ። በልማት ስም ወልደን ከከበድንበት ተፈናቀልን፤ አገራችን አደገች እያለ ሕዝብ በኑሮ ውድነት ተሰቃየ። በልቶ ማደር ብርቅ ነው። እንደሙጫ የሚያጣብቀንን ማህበረሰባዊ ትስስር በስልጣን ለመቆየትና ህብረተሰቡን ለመዝረፍ ሲል ሆን ብሎ እያፈራረሰው ነው:: ይኽ ሁሉ አይበቃንምን? ይኸ ሁሉ አይመረንምን?
ወላጆቼ፣ እህት ወንድሞቼ!ውርደት ይብቃን። የተረገጥንና የተገደልን አንሶን ፍጹም ማንንም ሊያሞኝ በማይችል የለበጣ ምርጫ ወደን የተረገጥን፤ ፈልገን የተገዛን ለማስመሰል ወያኔ የሚያደርገውን ሩጫ እናክሽፈው:: ከፊታችን ያለውን ምርጫ ባለመሳተፍ ምሬታችንን እንግለጽ።
Read more »
Posted by Unknown at 8:32 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Thursday, May 21, 2015

መሸነፍን በአሸናፊነት የተቀበሉ መሪዎች

“ሕዝብን መታዘዝ ይገባል!”
eth election
May 18, 2015 07:15 am By Editor Leave a Comment
በቅርቡ በሥልጣን ላይ እያሉ በምርጫ መሸነፋቸውን ባመኑበት ጊዜ ሥልጣናቸውን ያስረከቡት የናይጄሪያው ጉድላክ ዮናታን በአፍሪካ የ65 ዓመታት የምርጫ ዴሞክራሲ ጉዞ ከሚጠቀሱ ጥቂቶች መካከል አንዱ ሆነው ሰንብተዋል፡፡ ይህም ተግባራቸው በናይጄሪያ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ታላቅ ሥፍራ የሚሰጣቸው የፖለቲካ ሰው አድርጓቸዋል፡፡
በአፍሪካ በተካሄዱ በርካታ ምርጫዎች የሕዝብን ድምጽ በማክበር ሥልጣናቸውን ለተቀናቃኛቸው በማስረከብ የሕዝባቸውን ድምጽ ያከበሩ መሪዎች በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡ ሁሉንም ለአሁኑ ማቅረብ ባንችልም የተወሰኑት ተጠቃሾች እነዚህ ናቸው፡-
1. ኤደን አብዱላ ኦስማን ዳር (ሶማሊያ) – በተለምዶ ኤደን ዳር ተብለው የሚጠሩት እኚህ ፖለቲካኛ የሶማሊያ የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት ነበሩ፡፡ በሥልጣን በነበሩበት ጊዜ ሶማሊያን እኤአ ከ1960 እስከ 1967 መርተዋል፡፡ (በዚህ ጽሁፍ ላይ የሰፈሩት ዓመታት በሙሉ እኤአdaar ነው)
የሶማሊያ ወጣት ሊግ አባል በመሆን የፖለቲካ ጉዟቸውን የጀመሩት ዳር አገራቸው በ1960 ነጻነቷ ስትጎናጸፍ ስመጥር እየሆኑ በመምጣታቸው የሶማሊያ የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት በመሆን ተመርጠው ለ7 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ ሆኖም በ1967 በተደረገ ምርጫ በቀድሞው ጠ/ሚ/ር አብድራሺድ አሊ ሸርማርክ ተሸንፈው ሥልጣናቸውን በጸጋ አስረክበዋል፡፡ በዚህም በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለተመረጠ መሪ ሥልጣን በማስረከብ ከአፍሪካ የመጀመሪያ ተብለው ከሚጠቀሱት አንጋፋው በመሆን ታሪክ ሠርተዋል፡፡
2. ኬነት ዴቪድ ካውንዳ (ዛምቢያ) – ከነጻነት በኋላ ኬነት ካውንዳ የአገራቸው የመጀመሪያ ፕሬዚዳንት በመሆን ከ1964 እስከ 1991 መርተዋል፡፡ አገራቸው ከእንግሊዝ ቅኝ ነጻ ለመውጣት ባደረገችው ትግል ቀዳሚውን ሥፍራ በመያዝ የታገሉት ካውንዳ በሥልጣን ዘመናቸው የተቀናቃኝ ፖለቲካ ፓርቲዎችን በሙሉ አግደው የራሳቸው ፓርቲ ብቻ እንዲንቀሳቀስ ማድረጋቸው በታሪካቸው የሚነሳ አንዱ አሉታዊ ጉዳይ ነው፡፡
ሆኖም እኤአ በ1970ዎቹ በተከሰተው የነዳጅ ዘይት ቀውስ ጋር በተያያዘ የዛምቢያ ኢኮኖሚ ከፍተኛ ችግር ውስጥ በመግባቱ በካውንዳ አገዛዝ ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር መስሎ ቢታይም በተቃራኒው ፕሬዚዳንቱ በሥልጣን እንዲቆዩ ምክንያት ነው የሆናቸው፡፡ በሌላ ጎኑ ይኸው ቀውስ ውሎ አድሮ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት በአገሪቷ እንዲጀመርና ዛምቢያ ወደ ነጻ ምርጫ እንድትደርስ አድርጓታል፡፡Kaunda
በ1991 በተካሄደ ምርጫ የካውንዳ ተቀናቃኝ ሆነው የተወዳደሩት ፍሬዴሪክ ቺሉባ አሸናፊ ሆኑ፡፡ በዚህ ወቅት ካውንዳ የወሰዱት እርምጃ ዓለምን አስደመመ፤ አስደነቀ! ኬነት ካውንዳ ገና ከጅምሩ ምርጫውን ማጭበርበር ይችሉ ነበር፤ አላደረጉም፡፡ በወቅቱ በሥልጣን ላይ የነበሩ በመሆናቸው የምርጫውን ውጤት ወደፈለጉት አቅጣጫ እንዲሄድ ማድረግ ይችሉ ነበር፤ ይህንንም አላደረጉም፡፡ ከዚህ ይልቅ በምርጫ መሸነፋቸውን አምነው ተቀበሉ፤ ሥልጣናቸውን ሕዝብ ለመረጣቸው ቺሉባ አስረከቡ፤ ሕዝባቸውን አከበሩ፤ አገራቸውን ታደጉ!
3. ሩፒያ ብዌዛኒ ባንዳ (ዛምቢያ) – ኬነት ካውንዳ በጀመሩት የምርጫ ዴሞክራሲ ፈር ተከትለው ሥልጣን የያዙት መሪዎች በሥልጣን ላይ እያሉ በምርጫ ሲሸነፉ ሥልጣናቸውን ለማስረከብ ብዙም ሲቸገሩ አልታዩም፡፡ ምክንያቱም የካውንዳ ራዕይና ውርስ (ሌጋሲ) ለትውልድ የሚተላለፍ በመሆኑ ነው፡፡
Read more »
Posted by Unknown at 5:22 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Tuesday, May 19, 2015

Ethiopia’s newest party (Semayawi) takes on ruling juggernaut

May 19, 2015
(Reuters) The leader of Ethiopia’s newest opposition party hopes discontent among urban youth will win him support in a weekend election that could otherwise be a clean sweep for the ruling party in Africa’s most populous nation after Nigeria.
Ethiopia's newest party (Semayawi)
Over 36 million people have registered for the May 24 polls, the country’s first election since long-serving leader Meles Zenawi died in 2012.
His Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) has been in power for almost a quarter of a century, and faces no reasonable prospect of defeat – the current 547-seat parliament has just one opposition member.
Yilekal Getinet, chairman of the three-year old Blue Party, or Semayawi in Amharic, says it originally put forward 400 candidates but electoral authorities cut the list to 139.
Semayawi expects to win seats in the urban areas in spite of such obstacles.
“The people’s anger is increasing from time to time. By the strong opposition from the people and demands for further changes we may win in towns,” he said.
Semayawi, which wants less government involvement in the economy, sees itself as offering change in Ethiopian politics, with the vast majority of its members younger than 35.
Some 57 opposition parties are taking part in the polls but analysts say they present no real threat.
The opposition won an unprecedented 147 seats in an election 10 years ago but most of them did not join parliament, alleging the ballot had been rigged. Many of then spent two years behind bars on charges of inciting violence.
LOTTERY
Yilekal says over 50 party members have been detained by police, and accuses the government of unfairly allocating financial resources to the ruling party and depriving opposition parties of television air time, claims rejected by authorities.
Yilekal’s name will not be on the ballot after he was disqualified by the National Electoral Board of Ethiopia (NEBE), which ran a draw to pick candidates for 52 parties that had never taken part in an election.
NEBE chairperson Merga Bekana said most of Semayawi’s candidates had broken electoral rules by belonging to another party, adding the board had been tough on all sides.
Two ruling party members have been arrested in recent days on charges of breaking the law, Merga said, adding the environment was “conducive” to open politics.
Yilekal was not reassured. “There may be an increment in some numbers but that does not show that Ethiopia is in a democratic process. The whole process is deteriorating,” he said.
Posted by Unknown at 3:03 PM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Saturday, May 16, 2015

የእኛ ጉድ ተወርቶ አያልቅም ...

በነገው እለት May 17 ከአለም ሃብታም የምትባለው ትንሿ ሃገር ኖርዌይ የህገ መንግስት ቀኗን ታከብራለች። የኖርዌይ ህገመንግስት የጸደቀውና ለኖርዌይ ቅኝ ተገዢ ህዝብ በስራ ላይ የዋለው May 17, 1814 ቢሆንም አንድ ጥይት ሳይተኮስ ታላቅ ወንድሜ ከምትላች ከስዊዲን ቅኝ ግዛት ነፃ የወጣችው ግን እ.ኤ.አ 1905 ነው። በ 1905 ምንም ብሄራዊ ስሜት የሚፈጥር ግጭት ባለመፈጠሩ ዛሬ እንደ ነጻነት ቀን እንኳን አይከበርም። ከስዊዲን በፊት ኖርዌይ ለ500 አመታት በውጭ ንጉሶች ስትመራ ነበር። ኖርዌይ ከስዊዲን ነፃ የወጣችው በሪፈረንደም ሆኖ ከዴንማርክ የተሾመላትን ተወዳጁ ንጉስ ሆኩን ሰባተኛን Haakon VII, ተቀብላ ንጉሰ ነገሥት ለመሆን በቅታለች። የዛሬው በጣም ተወዳጁ ንጉስ ኖርዌይ በመወለድ 3ኛ ሲሆን አያቶቹ ግን የዴንማክ ንጉስ ትውልድ ናቸው።
እኛና ኖርዌይ .....
ኖርዌይ በጣም ድሃ ሃገር ስለነበረች በሁለቱ የአለም ጦርነቶች መሃከል (interwar period 1915-1939) በተለይ በ1922 በዋና ከተማዋ ኦስሎ በፓርላማው መግቢያ በር ፊት ለፊት በረሃብ የሚሞቱ ሰዎች ነበሩ። እ.ኤ.አ እስከ 1955 ድረስ ምግብ በራሽን ካርድ በቀበሌ ይሰጥ ነበር። ስኳር ቅንጦት ነበር። ኖርዌይ ከአውሮፓ ነገሥታት የ500 አመታት ቅኝ ግዛት በ1905 ነፃ በወጣች ጊዜ እኛ ነፃ ሃገር ነበርን። እነርሱ ነፃ የወጡት እኛ ነፃ ሆነን በምኒሊክ መሪነት ጣሊያንን ከኢትዮጵያ ከተባረረ ከ9 አመታት በኋላ ነው።
በ9 April 1940 አዶልፍ ሂትለር ኖርዌይን ወረረ። ከ20 000 በላይ የሚሆኑ ዜጎቻቸውን ገደለባቸው ሃገሪቷን በእሳት አቀጣጠላት። በ1945 ሂትለር በራሺያዎች ከተሸነፈ በኋላ League of Nations ፈርሶ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (United Nations) ሲቋቋም ኢትዮጵያ መስራች ሃገር ነበረች። February 1946 የመጀመሪያው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ የኖርዌዩ ተወላጅ Trygve Lie ነበር።
የሃይለ ስላሴ ብልህነት ...
በ1952 የተባበሩት መንግስታት ኤርትራ ከጣሊያን ነፃ ወጥታ ስለነበር እንዴት መተዳደር እንዳለባት ውይይት ሲካሄድ አፄ ሃይለስላሴ በአዶልፍ ሂትለር ለፈራረሰችው በችጋርና ጦርነት ለተጎዳችው ኖርዌይ ያልተጠበቀ የገንዘብ እርዳታ ያጎርፉ ጀመር። አፄ ሃይለስላሴ ይህን ያደረጉት ኤርትራን ከተባበሩ መንግስታት በአደራ ለመረከብ ስለፈለጉ ነበር። በወቅቱ ብቸኛዋ ከቅኝ ገዢዎች ነፃ የአፍሪካ ሃገርና የተባበሩት መንግስታት አባል ሃገር ኢትዮጽያ ለአንዲት ድሃ የነጮች ሃገር የምትሰጠው መጽዕዋት አስጋራሚ ሆኖባቸው ነበር። ለኖርዌይ እርዳታ እየሰጡ በጎን ደግሞ ንጉሱ የኖርዌይ ተወላጁ የተባብሩት መንግስታት ዋና ፀሃፊን Trygve Lieን ጠበቅ አድርገው በመያዛቸው (lobby) ኖርዌይ በተባበሩት መንግስታት ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴረሽን እንድትተዳደር በሚለው ውሳኔ ላይ ጥብቅና እዲቆሙ አደረጓቸው። በዋና ፀሃፊው ምርቃት ኤርትራ ለነጮች በድጋሚ በአደራነት ከምትሰጥ ከኢትዮጵያ ጋር በፈዴራል መንግስቷ ራሷን እንድታስተዳደር አደረጉ።
አሳፋሪው ትውልድ ...
ዛሬ ከወንድምና እህቶቻችን ጋር ያለያዩን ይባስ ብለው የኤርትራን ህዝብ እንደ ጠላት በ100 ሺህ ወታደር ድንበር በማስጠበቅ "ልማታዊ መንግስት" የሚሉትን ታሪክንና ብሄራዊ ጥቅምን የማያውቁ የክዱ መሆናቸውን እያየን ነው። ይባስ ብሎ 21ኛው ክፍለ ዘመን ይሄንን አገዛዝ እንደ መንግስት የሚደግፉ ደንቆሮዎችን ለማየት አብቅቶናል።
○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○ ○

ከየምታዩት ክሊፕ በ1954 ንጉሱ ለኖርዌይ ከሰጡትን የመቶ 150 000 ክሮነር እርዳታ አንዱን የሚያሳይ ሲሆን በ1955 ደግሞ የተባበሩት መንግስታት የኤርትራን የማስተዳደር ጉዳይ ለኢትዮጵያ መሰጠቱን ያሳያል። 
Source: Ethiopia at Bay: A Personal Account of the Haile Selassie Years
By John H. Spencer
ልጅ ግሩም's photo.
ልጅ ግሩም's photo.

Posted by Unknown at 2:17 PM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Tuesday, May 12, 2015

ከሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ! የስም ማጥፋት ዘመቻው ከጀመርነው ትግል ፍፁም አያንበረክከንም!

May 11, 2015
ሰሞኑን በህውሓት/ኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ባሉ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰማያዊ ፓርቲ ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዘመተ ያለውን የስም ማጥፋት ፕሮፓጋንዳ በአትኩሮት ሲከታተለው ቆይቷል፡፡ በዚህም የህዝብ ንብረት የሆኑ ሚዲያዎች፤ ለህዝብ አገልግሎትና በህዝብ ግብር በሚሰበሰብ ገንዘብ የሚተዳደሩ የማህበረሰቡ የአገልግሎት ተቋማት ጭልጥ ብለው የሰማያዊ ፓርቲ ስም በማጉደፍ እና በማብጠልጠል ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውን በትዝብት ተመልክተናል፡፡
Semayawi party to welcome Andinet members
ሰማያዊ ከተቋቋመ ጀምሮ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሱ በደሎችን በሀገርም ሆኖ በውጪ ሲፈፀም ዝም ብሎ የመመልከት ትዕግስት ኖሮት አያውቅም፡፡ ይህ በዋነኝነት ፓርቲው የተቋቋመለት መርህ ነው፡፡ በግራዚያኒ ስም ለሚሰራ ሃውልት ተቃውሞ ለማሰማት አስፈላጊውን የህግ መስፈርት አሟልተን ባለበት ሁኔታ በገዢው ፓርቲ ትእዛዝ አባላቶቻችን ተደበደቡ፡፡ በሳውዲ አረቢያ ውስጥ በወገኖቻችን ላይ ለሚደርሰው ኢሰብአዊ በደል ሰቆቃቸውን ለማሰማት በጠራነው ሰልፍ እንደገና በመንግስት ትእዛዝ አባላቶቻችን ላይ ድብደባና እስር ተፈጸመባቸው፡፡ በቅርብ በሊቢያ፣ በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም በየመን በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ የደረሰውን እጅግ ሰቅጣጭ እና በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ብሔራዊ ውርደት ሰማያዊ ፓርቲ አስቆጭቶታል፡፡ በዚህም የተነሣ እነዚህ በደሎች መድረሳቸው ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ በንቃት እየተከታተለ መረጃው ለህዝብ እንዲደርስ እያደረገ ጎን ለጎን መንግስት ለወገኖቻችን የድረሱልኝ ጥሪ አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥ ፓርቲያችን ሲያሳስብ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡
ሆኖም ይኸንን ዘግናኝ እና አረመኔያዊ ድርጊት ማውገዛችን እና መቃወማችን ከዛም አልፎ በወገኖቻችን ላይ የተፈፀመ ተግባር መከታተላችን ፓርቲው ሊያስመሰግነው ሲገባ ይልቁንም ገዥው ፓርቲ በተለያዩ የመንግሰት ሚዲያዎች የሰማያዊ ፓርቲ ስም ለማጠልሸት ሲሯሯጡ ማየት ትዝብት ውስጥ የሚጥል ብቻ ሳይሆን በህግም የሚያስጠይቅ ጭምር ነው፡፡ መንግስት ሃላፊነቱን እና ተግባሩን በመመርመር በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ብሔራዊ ውርደት ዳግመኛ እንዳይፈጸም ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ገዢው ፓርቲ ከሃገር ብሄራዊ ጥቅም ይልቅ የድርጅቱ ኢኮኖሚያዊ ትርፍ በልጦበት ለመቀበል ፈቃደኛ አልሆነም፡፡
Read more »
Posted by Unknown at 3:56 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Monday, May 11, 2015

Ethiopia-Crisis-and-Conflict-US-Aid


እንደ ኢትዮጵያ ከልመናና ከምጽዋት ጋር ስሙ የሚነሳ ብዙ አገር የለም። ላለፉት ሰላሳና አርባ አመታት የቆየ ሀቅ ነው። በችጋር ጊዜ መለመን ግድ ሊሆን ይችላል። ሁሌ መለመን ግን ህመም ነው። እኛ ግን ከልመና ጋር ከመለማመዳችን የተነሳ ይመስላል ፈጽሞ ሲረብሸን አይታይም። እንዲያውም የተመቸን ነው የሚመስለው። ፖለቲካችን ሁሉ ልመና ተኮር ነው። የአገሪቱ ዲፕሎማቶች ዋነኛ ስራቸው ተግቶ መለመን ሲሆን ሲሳካላቸው ‘በተደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ይህን ያህል ርዳታ ተገኘ’ ብለው በሚቆጣጠሩት ቲቪ ያውጃሉ። እንደ ድል ብስራት እኮ ነው የሚያዩት። አንዳንድ ተቃዋሚዎቻቸው ደግሞ ርዳታ እንዳይገኝ ማሰናከል (ማቃጠር በሉት) ላይ ተጠምደዋል። ሃያላን መንግስታትና እነሱው የሚቆጣጠሯቸው እንደ አለም ባንክ ያሉ ድርጅቶች ርዳታ እንዳይሰጡ መወትወት። እንዴት ያሳፍራል። ሁለቱም አቅመቢስነትን ከመቀበል ይመነጫሉ፤ እኛ ምንም ለማድረግ አቅም የለንምና ይሄን ስጡኝ ወይ ደግሞ ያን አትስጡብን እኮ ነው ነገሩ። ስለራስ አቅም ሳይሆን በሌላ ሰው ወይም አካል ቁጥጥር ስር ያለን ሀብት/አቅም አንጋጦ የማየት በሽታ ነው። ልመናውም ምጽዋት ማከላነሉም (ምቀኝነቱ) የጥገኝነት አባዜን ከማንጸባረቅ ባለፈ ግን አንድም ነገር አይለውጥም። የሞራል ጥያቄውን ብንተወው እንኳን በአለም ታሪክ በልመና ታሪክ የሰራ አገር የለም፤ ቢኖር ኖሮ ማን ይቀድመን ነበር? በአንጻሩ ምጽዋት ጠባቂነት አንድን ህዝብ ከልመና ለመውጣት ከሚያዳግትበት አዙሪት ውስጥ ሊቀረቅረው ይችላል። እዚያ አዙሪት ውስጥ አይደለንም ብሎ መናገር የሚቻል አይመስለኝም። ይህን አዙሪት ለመረዳት ሀብታሞች ለምን እንደሚረጥቡን መጠየቅ ያስፈልጋል።
Read more »
Posted by Unknown at 11:48 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Monday, May 4, 2015

Anti-Police Protest in Israel Turns Violent

TEL AVIV — A protest on Sunday by thousands of Ethiopian-Israelis and sympathizers against police harassment and brutality turned by nightfall into a chaotic and unusually violent confrontation with the police in the center of Tel Aviv.

The demonstration began peacefully in the afternoon with protesters blocking main thoroughfares of Tel Aviv, paralyzing the heart of the city for hours as officers looked on and stopped the traffic. Later, demonstrators hurled stones, overturned a police vehicle and clashed with the police in Rabin Square. Officers responded with stun grenades and water cannons.

About 46 people were slightly injured, half of them police officers, and at least 26 protesters had been arrested by midnight, according to the police.
Prime Minister Benjamin Netanyahu called for calm, saying, “All claims will be looked into but there is no place for violence and such disturbances.”
The police said that agitators had stirred up the atmosphere. Many here compared the cry of the young, angry generation of Ethiopian-Israelis who came out on Sunday to the tensions in American cities like Baltimore or Ferguson, Mo., that have been roiled by friction between blacks and the police.
Read more »
Posted by Unknown at 9:42 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Friday, May 1, 2015

አሜሪካ አይሲስን ለምን ፈጠረችው?

(ክንፉ አሰፋ)

ግብጽ የሃያ አንድ ክርስቲያን ዜጎችዋን በአይሲስ መታረድ ዜና እንደሰማች ዝም ብላ አልተቀመጠችም ነበር። ብሄራዊ የሃዘን ቀንም አላወጀችም። እንዲህ ነበር የሆነው። ከመቅጽበት ተዋጊ አውሮፕላኖችዋን አስነስታ ወደ ሊቢያ ላከቻቸው። የአይሲስ አራጆች የተከማቹበትን ደርና የተሰኘ ስፍራ እያከታተለች በቦምብ ቀጠቀጠችው። ብዙ አራጆች በድብደባው አለቁ። እንደ ግብጽ አጀማመር ቢሆን የሊብያው አይሲስ ክንፍ ድሮ-ድሮ ከምድረ-ገጽ ይጠፋ ነበር። ግና አልሆነም። አሜሪካ ጣልቃ ገባች። ግብጽ የአሜሪካን “ጸረ-ሽብር” ዘመቻ በማገዝዋ ምስጋና ማግኘት ሲገባት በተቃራኒው ተወገዘች። ከጥቂት ድብደባ በኋላ ፔንታጎን ግብጽን አስጠነቀቀ[0]። የኦባማ አተዳደርም ደብደባው በአፋጣኝ እንዲቆም ቀጭን መልእክት ላከ። ይህ ድርጊት ከዚህ ቀደም ስለ አይሲስ አፈጣጠር ኤድዋርድ ስኖደን[1] የለቀቀው ምስጢራዊ መረጃ ጋር ተዳምሮ በአሜሪካ ላይ የነበረውን ጥርጣሬው አጠናከረው።

ነገሩን ለማመን ያዳግት ይሆናል። በግልጽ የሚታዩ መረጃ እና ማስረጃዎች ግን ተአማኒነታቸው ጥርጥር ውስጥ የሚገባ አይደለም። “በአይሲስ እየታረዱ ያሉት ዜጎች የፊልም ቅንበር እንጂ እውነት አይደለም![2]” የሚሉ ባለሞያዎችም የትንተናቸው መነሻ ከዚህ ጉዳይ ጋር ይያያዛል።
ይህ አሸባሪ ድርጅት ስራውን ከጀመረ አንድ አመት ባልሞላ ግዜ ውስጥ ከመቶ ሺ በላይ ዜጎችን በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደለ ይናገራል። ቦምብ እንደዝናብ የሚወርድባቸው ሃገሮች፤ ሶማልያ፣ የመን፣ ኢራቅ፣ ሶርያ፣ አፍጋኒስታን፣ፓኪስታን… ተደምረው አይሲስ ከሚነግረን ግድያ ሩብ ያህሉንም አላደረጉም። የሃያላን ሃገሮች ምላሽ ግን በአፍ ከማውገዝ ያለፈ አለመሆኑ በአይሲስ አሰራር ላይ ተጨማሪ ጥርጣሬ ይፈጥራል።
Read more »
Posted by Unknown at 2:33 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest
Newer Posts Older Posts Home
Subscribe to: Posts (Atom)

About Me

Unknown
View my complete profile

G7PF

G7PF

Oppostion Group

  • Ginbot 7
  • DCESON
  • UDJ
  • Andinet
  • Semaywi party

NEWS AND VIEWS

  • ESAT
  • Ethiopian Review
  • ECADF
  • Ethiomedia

RADIO

  • DW.DE
  • VOA
  • ESAT
  • Addise dimits

HUMAN RIGHTS

  • HRW
  • LCRC
  • Amnesty

Ethiopia flag

Ethiopia flag

REYOT ALEMU

REYOT ALEMU

Free Andargachew Tsege

Free Andargachew Tsege

Free zone9 Bloggers

Free zone9 Bloggers

Free political prisoners in Ethiopia

Free political prisoners in Ethiopia

Total Pageviews

33,814

Blog Archive

  • April (1)
  • October (2)
  • September (4)
  • August (3)
  • July (5)
  • June (6)
  • May (9)
  • April (7)
  • March (12)
  • February (6)
  • January (20)
  • December (25)
  • November (33)
  • October (14)
  • September (4)
  • August (2)
  • July (5)
  • June (1)
  • May (4)
  • April (28)
  • March (24)
  • February (7)
  • January (3)
  • December (5)
  • November (14)
  • October (12)
  • September (12)
  • July (8)
  • June (2)
  • May (5)
  • April (4)
  • March (7)

victims 2005

victims 2005
Picture Window theme. Powered by Blogger.