Tuesday, April 29, 2014

ፖሊስ የጣይቱ ልጆችን ለማሸማቀቅ እየጣረ ነው

April 29, 2014
ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ለተደረገው ሰልፍ ቅስቀሳ ላይ እያሉ ፖሊስ ‹‹የእውቅና ደብዳቤው አልደረሰኝም፣ ህገ ወጦች ናችሁ!›› ብሎ ያሰራቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት (የጣይቱ ልጆች) ላይ ፖሊስ የተለያዩ የማሸማቀቂያ ስልቶችን እየወሰደ ይገኛል፡፡ በዛሬው ቀን ፖሊስ ታሳዎቹን በተለይም ሜሮን አለማየሁና ንግስት ወንዲፍራውን ‹‹እስር ቤቱን በመረበሽ›› በሚል ሌላ ክስ ከግቢ አስወጥተው ቃል ተቀብለዋቸዋል፡፡ በወቅቱም ማስፈራራትና ዛቻ እንደደረሰባቸው ታሳሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
የጣይቱ ልጆች በታላቁ ሩጫ ላይ በፖሊስ በተያዙበት ወቅት ፖሊስ የተለያዩ በደሎችን ለመፈጸም ሲጥር መብታቸውን ለማስከበር ባደረጉት ጥረት ፖሊሶች ሌሊት ከግቢ አስወጥተው የድብደባና ሌሎች ማስፈራሪዎችን እንዳደረጉባቸው ይታወሳል፡፡
በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ እስር ቤቶች የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ምግብ እንዳይገባላቸው፣ ቤተሰብ እዳይጠይቃቸውና ሌሎችንም መብታቸውን የሚጋፉ በደሎች እየተፈጸሙባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያYoung semayawi party female activists
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/12050/

Monday, April 28, 2014

ጥቂት ስለ ማዕከላዊ! (አክመል ነጋሽ)

April 27, 2014
ማዕከላዊን በከፊል አውቀዋለሁ፡፡ ትናንት ሰባት የሚሆኑ ጋዜጠኞች፣ ብሎገሮችና አክቲቪስቶች መታሰራቸውን ተከትሎ ወደ ማእከላዊ መወሰዳቸውን ሰምተናል፡፡ በቀጣዮቹ ቀናት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ጨለምተኛ ልመስል እችል ይሆናል፤ እውነታው ግን ይኸው ነው፡፡
መጀመሪያ ክሱ ምን ሊሆን ይችላል የሚለው አጓጊ ጥያቄ ነው፡፡ ይህን ለማወቅ ወሳኝ ፍንጭ የሚሰጠው የቤት ፍተሻው ነው፡፡ የታሰሩትን ሰዎች ቤት የሚፈትሹት ፖሊሶችና መርማሪዎች ቤቱን የሚፈትሹት ለጥቂት ሰዓታት (ቢበዛ ለሁለት ሰዓታት) ከሆነና በጣም ብርበራ ያልበዛበት ከሆነ አለቆች በጸረ ሽበር ሕግ ለመክሰስ እንዳላሰቡና አስፈራርተው ብቻ በዋስ ለመልቀቅ እንዳሰቡ ፍንጭ ይሰጣል፡፡ በተቃራኒው ፍተሻው በትንሹ ከስድስት ሰዓታት በላይ የሚረዝምና በቤቱ የተገኘውን ወረቀት፣ መጽሐፍ፣ ሲዲ፣ ኮምፒውተርና ሞባይሎች ምንም ሳይስቀሩ ሰብስቦ የሚያስኬድ ከሆነ ጉዳዩ በጸረ ሽብር ሕግ ከመክሰስ ጋር የተያያዘ እንደሆነ መጠርጠር ያሻል፡፡
ይሄ የቤት ፍተሻ የቤቱን ኮርኒስ መቅደድና ወለሉን እስከመቆፈር ይደርሳል፡፡ በዚህ ጉዳይ ውስጥ ዋናው ግንዘቤ መወሰድ ያለበት ነገር ሰዎቹ የሚያስሩት ማስረጃ በመያዝ ሳይሆን፤ ማስረጃ ሊሆን የሚችል ማንኛውም ነገር በፍተሻው አግኝቶ እሱን ቀባብቶና አሳምሮ መክሰስ መቻላቸው ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ መርማሪዎች፣ አቃቢ-ሕጎችና ተሰያሚ ዳኞች ተገናኝተው እንዲያወሩ ስለሚደረግ ነገሩን ፍርድ ቤት አድርሶ የሚፈለገውን ውሳኔ ለማስወሰን መንገዱ ጨርቅ ነው፡፡
በማእከላዊ ከተወሰዱ በኋላ ቢያንስ ለሦስት ቀን ያህል ከቤተሰብም ሆነ ከማንም ጋር መገናኘት የማይተሰብ ነው፡፡ ይህ ታሳሪዎቹንም ሆነ ቤተሰቦቻቸውን የበለጠ ለማደናገጥና የሥነ-ልቦና ጫና ውስጥ ለመክተት ወሳኝ ነው፡፡ ታሳሪዎቹ በቀጥታ የሚወሰዱት ‹‹ጣውላ ክፍል›› ወደሚባሉ የእስር ክፍሎች ነው፡፡ በዚህ ክፍል የሚታሰሩ ሰዎች በ24 ሰዓት ውስጥ ለ15 ደቂቃ ያህል የሚቆይ ጸሀይ መሞቂያና መጸዳጃ ቤት መሄጃ ፈቃድ ይሰጣቸዋል፡፡ እነዚህ ከፍሎች በግምት አራት በአራት ስፋት ያላቸውና ወለላቸው ከጣውላ ጣሪያና ግድግዳቸው ከኮንክሪት የተሠራ ሲሆን፤ ቦታው ሻል ካለው የእስር ኮሪደር ‹‹ሸራተን›› እጅግ ያነሰ ነጻነት ያለውና፤ በጣም ከባሰው ጨለማ ክፍል ‹‹ሳይቤሪያ›› የተሻለ ቦታ ነው፡፡ ምርመራው ለእስር በገቡበት ምሽት ይጀመራል፡፡ የኢ-ሜይልና ሌሎችም አካውንቶች ፓስወርዶች በግድ እንዲሰጡ ይደረግና የኮምፒውተር ሀ ሁ በማያውቁ ‹‹መርማሪዎች›› አካውንታቸው ይበረበራል፡፡
ከዚሁ ጎንለጎን ቀለል ያለ ምርመራና ጥያቄና መልስ ይካሄዳል፡፡ በቀጣዮቹ አምስት እና አስር ቀናት ‹‹ጠቃሚ ውጤት በምርመራ አላገኘንም›› ብለው ካሰቡ ወደ ሌላኛው የእስር ክፍል ወደ ‹‹ሳይቤሪያ›› ያዘዋውሯቸዋል፤ በዚህ ወቅት የምርመራ ስልቱና አጠቃላይ ሁኔታውም ይለወጣል፡፡ ታስረው መቆየት ‹‹አለባቸው›› ወይም ‹‹የለባቸውም›› የሚለውን የሚወስኑት በዚህ ጊዜ ነው፡፡ ውሳኔው ይፈቱ ከሆነ ወደ ‹‹ሸራተን›› የእስር ክፍል ያዘዋውሯቸዋል፡፡ ይህ ከቤተሰብ ጋር መገናኘት የሚያስችል የእስር ቦታ ሲሆን፣ በጊቢው ካሉት የእስር ክፍሎች ሁሉ የተሻለ አንጻራዊ ‹‹ነጻነት›› ያለው ነው፡፡
በጥቅሉ ሳይቤሪያ ከአንድ ሜትር ስኩዌር ብዙም የማይበልጥ፣ ጨለማ፣ በጣም ቀዝቃዛና አምስት ቀናት ቢቆዩቡት መላው አካልን ወደ አመድነት (ነጭነት) የሚለውጥ ዘግናኝ ቦታ ነው፡፡ በዚህ እስር ክፍል ውስጥ ሰዎች የሚታሰሩት ያላደረጉትን ነገር አድርገናል ብለው እንዲያምኑ ወይም የያዙትን ‹‹ሚስጥር›› ‹‹እንዲያወጡ›› ነው፡፡ በዚህ ክፍል የሚታሰሩ እስረኞች አንዳንዴ ያልተቋረጠና እስከ 14 ሰዓት የሚደርስ ምርመራ በፈረቃ በሚቀያየሩ መርማሪዎች ይደረግባቸዋል፡፡ በምርመራው እንደ እስረኛው ሁኔታ የሚላላና የሚጠነክር ድብደባና ቶርች መጠቀም የተለመደ ‹‹አሠራር›› ነው፡፡ ቶርች የተደረጉ ሰዎች ቁስላቸው እስከሚያገግም ከቤተሰብም ሆነ ጠበቃ ጋር ማገናኘት የማይታሰብ ነው፡፡ በእነዚህ ሁሉ ወቅቶች ቤተሰብ ምግብ ለማድረስ፣ ጠበቆች ደንበኞቻቸውን ለማግኘት የሚደርጉት ጥረት ውጤት አልባ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ይቺ ነች፡፡

By Akemel Negash
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/12025/

Sunday, April 27, 2014

ከኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ(ኢጋመ) የተሰጠ መግለጫ፣ የጋዜጠኞቹና የአክቲቪስቶቹ እስር አሳሳቢ ነው፡

April 26, 2014
ትላንት ሚያዝያ 17 2006 አመሻሽ ላይ ዞን 9 በተሰኘ ድረ ገጽ (ብሎግ) ላይ በሳል ፖለቲካዊና ማህበራዊ ትችቶችን በማቅረብ ከሚታወቁት ፀኀፍት መሀከል 7 ቱ (ማህሌት ፋንታሁን በፍቃዱ ሀይሉ Ethiopians journalists forumናትናኤል ፈለቀ ዘላለም ክብረት አጥናፍ ብርሀነ አቤል ዋበላ ኤዶም ካሳዬ) እና የአዲስ ነገር ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉ ይታወቃል፡፡ ግለሰቦቹ በተለያየ ቦታ በየስራ ገበታቸዉ ላይ እያሉ ሁሉም በተመሳሳይ ሰዓት በፀጥታ ሀይሎች ተይዘዉ ማዕከላዊ ምርመራ ማዕከል ታስረዉ የሚገኙ ሲሆን፤ የተለያዩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት እስሩ በደንብ የታሰበበት ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ታሳሪዎቹ ታሰሩ ከተባለበት ሰዓትና ደቂቃ ጀምሮ የሚገኙበትን አጠቃላይ ሁኔታ ለማጣራት አየሰራ ሲሆን ፤ እስካሁን በሰበሰበዉ መረጃ መሰረት ልጆቹን ለእስር የሚያበቃ ምን አይነት ማስረጃ እንደተገኘባቸው ለማወቅ አልቻለም፡፡
ሆኖም ግን ለእስር ከመዳረጋቸው በፊት ከመንግስት ሲርስባቸዉ በነበረዉ ህገወጥ ድርጊቶች ምክንያት ለረጅም ጊዜ ስራቸዉን ካቋረጡ በኋላ በቅርቡ ወደ ስራ መመለሳቸዉን ይፋ አድርገው እንደነበር ከድረገጻቸው ላይ ለመረዳት ችለናል፡፡ ይህ ጉዳይ እስሩን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎብናል፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ መንግስት ታሳሪዎቹን ለማሰር ያበቃዉ ተጨባጭ ማስረጃ ካለ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ፤ ያ ካልሆነ ግን እስረኞቹን በአስቸኳይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቅ እናሳስባለን፡፡
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/12016/

የመለስ ዜናዊ ፲ ታላላቅ የአፍ ወለምታዎች


የዞን ዘጠኝ ነዋሪዎች የሆኑት በፈቃዱ ዘ ኃይሉ የመለስ ዜናዊ ‘ሀሁ’ በስልጣን ጎዳና እንዲሁም ዘላለም ክብረት መለስ ወደ ውጭ - መለስ ከውጭበሚል ርዕስ ሁለት ጦማሮች አስነብበውናል፡፡ ይህም ስለጠቅላያችን የጤና ሁኔታ ከነበረው ውዝግብ መለስ ብለን ሌሎች ሁኔታዎች እንድንቃኝ ዕድል ሰጥቶናል ፡፡ዛሬ ቀኑ ቅዳሜ ነው፤ እሰኪትንሽ ቅዳሜ ቅዳሜ የሚሸት ነገር እያወራን ዘና እንበል በሚል ደግሞ ይችን ጽሑፍ ከዱራሜ ዶት ኮም ያገኘነውን የጠቅላያችንን አስር ታላላቅ የአፍ ወለምታዎች ፣ በዚህ ንግግራቸው የተገረመው አብዛኛው ሰው ወደሚሰማው ቋንቋ እንደወረደ ተርጉመን ለአደባባይ አውለነዋል፡፡


፲. በ1983  ዓ.ም. በለንደኑ ጉባዔ  በኢህአዴግ ታርጋ የተሰባሰቡት ቡድኖች የፓርቲያቸው ህወሓት ተቀጥላ እንደሚሆኑ ለአሜሪካና ብሪታኒያ ባለስልጣናት አረዷቸው፡፡ብሪታኒያውያኑ ይህንን በተቃወሙ ጊዜ ቁጣቸው በግልጽ የሚታየው አቶ መለስ እንዲህ አሉ፡፡

     “አንድ ነገር ግልጽ ላድርግ  ፤ ከጉባዔው በኋላ  ኢህአዴግ የሚባል መንግስት አይኖረንም፡፡”

           
፱.  በ1985/6  ዓ.ም. ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ ያላቸውን እይታ በአንድ ቃለ መጠይቅ ማብቂያ ላይ እንዲያካፍሉ ከአንድ ዘጋቢ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ መለስ እንዲህ ሲሉ መለሱ፡፡

     “የኢትዮጵያ ዕድሜ መቶ አመት ብቻ ነው ፤ከዚህ በቀር ሌላ  የሚያወሩት ራሳቸውን በተረት ተረት እያሞኙ ነው፡፡" 

፰. በ1986/7 ዓ.ም. አስመራ ከተማ ውስጥ  ለአንድ የውጭ ሀገር ጋዜጠኛ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ስለ ኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

    “ከኢሳይያስ ጋር አንድ ሰዓት ማሳለፍ፣ 10 መጽሐፍ ከማንበብ በላይ ልበብሩህ፣ አዋቂ እና ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡”

፯. ለአምስት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያን ታሪክ ካጠኑት ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን ጋር በ1989 ዓ.ም.  በነበራቸው ወይይት ከምንሊክ ወረራ በፊት ኢትዮጵያ የምትባል አንዲት  አገር እንዳልነበረች ተናገሩ፡፡ይህ የበለጠ አጽንኦት ለመስጠት ሲሞክሩ እንዲህ አሉ፡፡

      “ትግሬዎች የአክሱም  አላቸው ፤ ይህ ለጉራጌ ምኑ ነው? አገዎች ላሊበላ  አላቸው ፤ ይህ ለኦሮሞ ምኑ ነው? ጎንደሬዎች ቤተ መንግስት አላቸው፤ ይህ ለወላይታ ምኑ ነው?”

፮. ለመንግስት ሚዲያዎች በሰጡት አንድ ቃለ መጠይቅ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ከጨርቅነት የዘለለ ምንም እንዳልሆነ ተናገረዋል፡፡

      “ባንዲራ የጨርቅ ቁራጭ ነው”

፭. በ1990 ዓ.ም. ሰማኒያ ሺ የሚደርሱ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ኤርትራውያንን ሀብት ንብረታቸውን ቀምተው  ኢ-ሰብዐዊ በሆነ መልኩ ከሀገር ካስወጡ በኃላ ለፓርላማው እንዲህ አሉ፡፡

      “የአይናቸው ቀለም ካላማረን ፣ ከሀገራችን የማባረር መብት አለን፡፡”

፬. በ1993 ዓ.ም. ልጇ ወደ ኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ዘምቶ አለመመለሱ ያሳሰባት  እናት ልጇ ወዴት እንዳለ መለስ ዜናዊን  አጥብቃ ጠየቀች፡፡በጥያቄዋ ድምጸት የተበሳጩት አቶ መለስ እንዲህ ሲሉ መለሱ፡፡

      “ሴትዮ፣ ልጅሽ በስድስት ወራት  ወደቤቱ ካልተመለሰ ፣ መልሱን ታውቂዋለሽ፡፡”

፫. በ1997 ዓ.ም. ምርጫን ተከትሎ በተካሄደው  ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ  በጠቅላያችን ትዕዛዝ 193 ያልታጠቁ ንጹሐን ዜጎች በአዲስ አበባ እንዲገደሉ ትዕዛዝ  ሲሠጡ የትግራዋይ ተወላጅ ለሆነው ለታማኛቸው ጄኔራል ሳሞራ አማራዎችን ለማለት አህዮች የሚለውን ቃል ተጠቅሟል፡፡

      “እነዚህ አህያ አማራዎች  ትምህርት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ሰላማዊና  ሃይማኖተኛ  የሚሆኑት ክላሽንኮቭ ስትደግንባቸው ብቻ ነው፡፡”

፪. ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ የከሸፈ ፣ ተከተታይ ወረራ   በ1998 ዓ.ም.  በሱማሊያ መሬት ላይ መሬት ያዛ በነበረበት ሰዓት ለ ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ አላማቸው የኢስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረትን ለማንበርከክ ሳይሆን በዚያ የሌሉትን በሱማሊያ የሚገኙት የኤርትራ ወታደሮች ለማሰደድ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

     “እያጠቃን ያለነው   በሱማሌ ወይዛዝርት ቀሚስ ስር  የተሸሸጉ የኤርትራ ኃይሎችን ብቻ ነው፡፡”


፩. በ2002 ዓ.ም. ከሊቢያው አምባገነን ሙዐመር ጋዳፊ ጋር ስለ ሁለትዮሽ ግንኙነት በሚወያዩበት ጊዜ አቶ መለስ እንዲህ አሉ፡፡

       “እኔ የመናዊ ነኝ ፤ የመናዊ እንደሆንኩኝ አውቃለው ፤ ሁላችንም የመናውያን ነን፡፡ ከነገሥታቱ  ቤተሰብ በቀር ሁላችንም አረብ ነን፡፡”
Link:-http://zone9ethio.blogspot.no/2012/07/blog-post_21.html

Saturday, April 26, 2014

Six bloggers, journalist detained in Ethiopia on Friday

April 26, 2014
One journalist and six bloggers in Addis Ababa, Ethiopia are detained last night (Friday April 25, 2014), their family members and colleagues reported.
Tesfalem Weldeyes, freelancer for the weekly English newspaper, Addis Fortune, and Addis Standard magazine was escorted from his house around known as ‘Gotera condominium’ by the police, according to his neighbor with whom he left his house key.
“Late this evening I got a massive knock at my door. I opened and the guy by the door screamed at me “Tesfalem is calling for you outside”. I thought maybe he got into accident and run out to his place. He was surrounded by about seven people dressed civil and two policemen. They are carrying some clothes in a plastic bag and papers in another. ‘You have a spare key to his house. If anything is taken from his place you will be accountable,’ one of them screamed at me,” his neighbor wrote on her facebook wall late last night.
This morning photographs of six bloggers, known as writers of Zone Nine who criticize the government, published on social media by their friends indicating that they all are also arrested last night.
zonenine
Campaign for the release of the detainees has also started on social media by their friends. They indicated that bloggers and activists arrested last night are: Befekadu Hailu Expert at St. Mary’s University College, Natnail Feleke, HR management officer at Construction and Business Bank; Mahlet Fantahun, Data Officer, Atnaf Berhane IT Services professional, Zelalem Kibret, Lecturer at Ambo University and Abel Wabella, a Tooling Engineer at Ethiopian Airlines.
According to relatives the detainees are now held in Maakelawi, a prison in Addis Ababa known mostly for interrogating detainees. Neither the police nor the government officials have made any statement on the issue to the media so far about the arrest of the journalists, bloggers and activists. Meanwhile the detainees are expected to appear to court by Monday.
“Tesfalem like anybody else have opinions…but he has never let them influence his articles and he always reached out to all parties in order to include a wide range of views; I remember how hard he fought to get into the ruling party’s latest congress. I am absolutely uninterested to hear what trumped up charges the government has to justify his arrest, he should be freed immediately!,” said former Associated Press correspondent in Ethiopia commenting on his facebook wall.
Another relative named Adam Brookes also wrote describing Tesfalem as “an independent journalist, a modest, much-loved individual who survived the 2010 Kampala bombings, and who reports with professionalism and insight on EPRDF rule in Ethiopia.”
In a related development one of the emerging opposition party known as blue Party has called for a public rally in Addis Ababa for tomorrow (Sunday).
“…the most significant human rights problems are: freedom of expression, freedom of association, illegal detention; displacement of certain ethnic groups, politically motivated trials; harassment; intimidation of opposition members and journalists, and continued restrictions on print media are just a handful of the violations.”
“Blue Party does not believe that the Ethiopian regime is willing to facilitate a political atmosphere that will provide freedom for the people. Therefore we believe we have to fight for it,” the party said in its statement a few minutes ago.
Link:-http://abbaymedia.com/2014/04/26/six-facebook-bloggers-journalist-detained-in-ethiopia-on-friday/

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለሚዲያ ማህበረሰቡ የተላለፈ ጥሪ

April 26, 2014

ውድ የሚዲያ ማህበረሰብ አባላት፡- ባለፉት 23 ዓመታት ህወሓት/ኢህአዴግ በህገ መንግስቱ የሚዲያ ነጻነት እንደሚፈቀድ ቢደነግግም በተግባር ግን የራሱን ፕሮፖጋንዳ ከሚነዛባቸው ሚዲያዎች ውጭ ሌሎቹን ሲዘጋና ሲያሸማቅቅ ኖሯል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ህዝባችን ከገዥው ፓርቲ ፕሮፖጋንዳ ውጭ አማራጭ መረጃ ማግኘት አልቻለም፡፡ ጋዜጠኞች እየታሰሩ፣ እየተሰደዱ፣ ሚዲያዎች እየተዘጉም ቢሆን የተቻላችሁን ያህል ለህዝብ መረጃ ለማድረስ የሚዲያው ማህበረሰብ አባላት ለምታደርጉት ሁሉ ከፍ ያለ ክብር አለን፡፡ የታፈነውን የህዝብ ድምጽ ለማሰማት የምታደርጉትን ጥረትም እናበረታታለን፡፡ ሆኖም አሁንም ቢሆን በገዥው ፓርቲ አፋኝነት ምክንያት ህዝባችን የሚገባውን መረጃ እያገኘ አይደለም፡፡ እናንተም በሰበብ አስባቡ ጫና እየደረሰባችሁ እንደሆነ ፓርቲያችን ይገነዘባል፡፡
Ethiopia's Semayawi (Blue) party logo
ገዥው ፓርቲ ላይ የሰላ ትችት የሚያደርሱ ጋዜጠኞች ‹‹አሸባሪ›› ተብለው ታስረዋል፡፡ ጋዜጦችና መጽሄቶች በስርዓቱ ተዘግተዋል፡፡ በርካታ ጋዜጠኞች አገራቸውን ጥለው ተሰደዋል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ድብደባ፣ ማስፈራሪያና ዛቻ ደርሶባቸዋል፡፡ እየደረሰባቸውም ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ በሚያደርስባቸው ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ ጫና ከገበያ ወጥተዋል፡፡ በአጠቃላይ በአሁኑ ወቅት ለህዝባችን አማራጭ መረጃ የሚያደርሱ ሚዲያዎችና የሚዲያው ማህበረሰብ መብቶቻቸውን ተነጥቀው አደጋ ላይ ወድቀዋል፡፡
አማራጭ መረጃ ለዴሞክራሲና ለልማት ቀዳሚውን ሚና እንደሚጫወት የሚያምነው ፓርቲያችን ይህን የመብት ረገጣና አፈና ሲቃወምና ሲታገል ቆይቷል፡፡ አሁንም በጠነከረ መልኩ ይቃወማል፡፡
ፓርቲያችን ሀሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ የተነጠቁትን መብቶቻችን ለማስመለስ በመጣሩ አመራሮቹና አባላቱ በህገ ወጥ መንገደ እስር ቤት በሚገኙበት ተመሳሳይ ወቅት የዞን ዘጠኝ ወጣቶች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህም ከመቸውም ጊዜ በላይ ጭቆናው እንደመረረ እና ሁሉን ማህበረሰብ ያቀፈ ትግል እንደሚያስፈልግ ዋነኛ ማሳያ ነው፡፡ ከዚህ የመረረ ጭቆና ህዝባችንን ነጻ ማውጣት የምንችለው እኛ ህዝቡን ማደራጀትና ማንቀሳቀስ የሚዲያ ማህበረሰቡም መደረጃውን ለህዝባችን ማድረስ ሲችል ብቻ ነው፡፡
ፓርቲያችን ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ጨምሮ ገዥው ፓርቲ ከኢትዮጵያውያን የነጠቃቸውን መብቶች ለማስመለስ ተቃውሞ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ የሚዲያው ማህበረሰብ ይህን የተቃውሞ ሰልፍ ሂደት ለህዝብ በማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የታመነ ነው፡፡ በመሆኑም መብቶቻችን በህዝብ ትግል ይመለሱ ዘንድ እናንተም የተለመደው የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡
መረጃ ኃይል ነውና በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ የህትመትም ሆነ የብሮድካስት ውጤቶች የተነጠቁትን መብቶቻችን፣ የሰላማዊ ሰልፉን ሂደት፣ በሂደቱ በፓርቲያችንና በህዝቡ ላይ የሚደርሰውን በደል እና ሰላማዊ ሰልፉን ለህዝብ በማድረስ ግዴታችሁን እንድትወጡ አደራ እንላለን፡፡ በተለይ ሌሎች ሚደያዎች በታፈኑበት በአንጻራዊነት የህዝብ ድምጽ በመሆን ላይ በሚገኘው ፌስ ቡክ በኩል መረጃዎችን ለህዝብ በማድረስ ቀላል የማይባል ጫና መፍጠር የሚቻል በመሆኑ አጋጣሚውን በመጠቀም መብታችን ለማስመለስ እንድንታገልና በሰልፉም እንድንገኝ አደራችን እናስተላልፋለን፡፡
ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፈንታ እንወስን!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/11957/

Friday, April 25, 2014

ሰበር ዜና፣ ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ማሰሩን ቀጥሏል

April 24, 2014
በዳንኤል ሃረጋዊ
Semayawi party members on action
ፖሊስ ቀስቃሾቹን እያሰረ ነው ፖሊስ የእውቅናው ደብዳቤ አልደረሰኝም በሚል በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የተሰማሩትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እያሰረ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬ ሲቀሰቅሱ የነበሩ ወጣቶች በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡ ቀስቃሾቹ ሰልፉ እውቅና እንደተሰጠው የሚያመለክተውን ወረቀት ለፖሊስ ቢያሳዩም ፖሊሶች የእውቅናው ደብዳቡ አልደረሰንም በሚል አስረዋቸዋል፡፡ ቀስቃሾቹ የያዙት የእውቅና ደብዳቤ ግልባጭ ለፖሊስ የተጻፈበት በመሆኑ ሰልፉ እውቅና አግኝቶ እያለ ሆን ተብሎ ለማደናቀፍ እንደሆነ ምክትር ሊቀመንበሩ አቶ ስለሽ ፈይሳ ገልፀዋል፡፡
በላም በረት፣ ቦሌ ድልድይ፣ ኮተቤ፣ መገናኛ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ቅስቀሳቸውን በተሳካ መልኩ አጠናቀዋል፡፡ በሌሎች አካባቢዎች የተሰማሩት አባላት ቅስቀሳውን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ በሌላ በኩል በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬን ጨምሮ በሌሎች የከተማይቱ ክፍሎች ፖሊስ ከ20 በላይ አባላትን ማሰሩ ታውቋል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ ፖሊስ ቅስቀሳው ላይ ያልነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንም እያሰረ ነው፡፡ የታሰሩትን አባላትና ደጋፊዎች ሁኔታ ለማጣራት ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ያቀኑ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ፖሊስ አስሯቸዋል፡፡
በዛሬው ቀን ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት
1. ብሌን መስፍን
2. አስናቀ በቀለ
3. መስፍን
4. ተስፋዬ አሻግሬ
5. እዮብ ማሞ
6. ኩራባቸው
7. ተዋቸው ዳምጤ

የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች
1. ፍቅረ ማሪያም አስማማው
2. እያስፔድ ተስፋዬ
3. ጋሻው መርሻ
4. ተስፋዬ መርኔ
5. ሀብታሜ ደመቀ
6. ዘሪሁን ተስፋዬ
7. ጌታነህ ባልቻ
8. ንግስት ወንዲፍራው
9. ሜሪን አለማየሁ ናቸው

የካ አካባቢ ታስረው የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ምግብ እንዳይገባላቸው ተከልክለዋል፡፡ በሌላ በኩል አህመድ መሃመድ፣ሀይለማሪያም፣ ሱራፌልና አምሃ የተባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መገናኛ አካባቢ ተይዘው ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ተዘዋውረዋል፡፡ በአጠቃላይ የካ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት 14 መሆናቸው ታውቋል፡፡ በሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች የሚገኙት አመራሮችና አባላት በአሁኑ ወቅት ቃል እየሰጡ ሲሆን ሊያድሩ እንደሚችሉም ተነግሯቸዋል፡፡
በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ቢሮ ተደውሎ የሰላማዊ ሰልፉን አስተባባሪዎች ጧት ሁለት ሰዓት ላይ ‹‹ኑ እና እንነጋገር!›› የሚል ጥሪ አድርጓል፡፡ ከሰልፉ አስተባባሪዎች መካከል አቶ ጌታነህ ባልቻ ታስሮ ይገኛል፡፡
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/11947/

Monday, April 21, 2014

ቴሌፎኑ ‘ለግዜው’ ጥሪ አይቀበልም

April 21, 2014
ክንፉ አሰፋ
“የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።…” የምትለዋ አሰልቺ የቴሌ መልእክት ያላጋጠመው ቢኖር ወደ ኢትዮጵያ ስልክ ደውሎ የማያውቅ ሰው ብቻ መሆን አለበት። ኮ/ል መንግስቱ ሃይለማርያም ወደ ቀድሞ ወዳጆቻቸው መደዋወል ጀመሩና በመሃል ተስፋ ቆረጡ አሉ። አስር ለሚያህሉ አርሶአደሮች እና የሰራዊቱ አባላት ዘንድ ደውለው አልተሳካለቸውም። ለሁሉም ጥሪ ያገኙት ምላሽ “የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።” የሚል ሲሆንባቸው ራሳቸውን ነቀነቁ። ሰው ሁሉ የጨከነባቸው መሰላቸው። እንዲህም አሉ። “የሃገሬ ሰው እንኳን የስልክ ጥሪ፤ የእናት ሃገር ጥሪስ መች ተቀበለ።”
ለአመታት በተከታታይ በሁለት ድጅት እያደገች ያለች ሃገር የስልክ መስመር ችግር ይገጥማታል ብሎ ማሰብ ይከብዳል። ችግሩን በደንብ ላልተረዳው፣ ሰው የሞባይል ስልክ የሚገዛው እንዲሁ ይዞ ለመታየት ነው ያስብል ይሆናል። ይህ አባባል በከፊል ትክክል ነው። ዘመናዊ ስልክ በመያዝ ለላንቲካነት ብቻ የሚጠቀሙበት ሰዎች አይጠፉም። የቻይናው ቀፎ ከሞዴል አርሶ አደሮች አልፎ ተራው አርሶ-አደር እጅ ላይም ገብቷል። አብዛኞቹ ግን ተንቀሳቃሽ ስልካቸውን አይጠቀሙበትም። ለዚህም ይመስላል በርካታ ተንቀሳቃሽ ስልክ የሚይዙ ሰዎች እንዲሁ ለእይታ እና ለላንቲካ ብቻ የሚመስላቸው። አገልግሎቱን በተመለከተ ግን 99 በመቶ የሚሆነው ችግር የመዋቅር ችግር ነው።
ለዓውዳመቱ ወደ ኢትዮጵያ ስልክ የደወላችሁ ካላችሁ፤ ይህ ነገር እንደገጠማችሁ እርግጥ ነው። ዘንድሮ ደግሞ ቴሌ ከፍቷል። የሞባይሉ መስመርማ እንደ አይን እልም ብሎ ነው የጠፋው። ከበርካታ ሙከራ በኋላ መስመር ያገኘ ሰው ካለ በደስታ ይዘልላል። የተቀባዩም ስልክ ካቃጨለ ተዓምር ነው የሚባለው። ከርማ ብቅ እንደምትለው የአዲስ አበባ መብራት… ልክ እንደ ቧንቧ ውሃ፤ ስልኳም “መጣች – መጣች!” ብሎ መጨፈሩ አይቀርም።
Ethio Telecom the worst service in Africa
“እንኳን አደረሳችሁ!” ለማለት እኔም ወደ ሃገር ቤት ስልክ መታሁ።
“የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።” የሚል መልስ ነበር ያገኘሁት። ለሁለተኛ ግዜ ስሞክር ደግሞ “የደወሉት ስልክ ለግዜው ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ ነው።” የሚል ምላሽ አገኘሁ። ደቂቃ ባልሞላ ግዜ ውስጥ ጥሪ ያማይቀበለው ስልክ ከአገልግሎት መስጫ ክልል መውጣቱ አስገረመኝ። ተስፋ ሳልቆርጥ ደገግሜ ሞከርኩ። ቢያንስ ከአስር ግዜ ሙከራ በኋላ፤ መስመር አገኘሁና ሎተሪ የወጣልኝ ያህል ተሰማኝ።
ደስታዬ ግን ብዙም አልዘለቀም። በመሃል እንግዳ ነገር ተፈጠረ። ስልኩን የተቀበለኝ የደወልኩለት ሰው አልነበረም። የተፈጠረው ክስተት – ባለንበት የመረጃ ዘመን እንደ 17ኛው ክፍለዘመን “ቴሌ በኦፐሬተር መስራት ጀመረ እንዴ?” ያሰኛል። ነገሩ ግን ሌላ ነው። ስልኩን ያነሳው የተለመደው የስልክ ጠላፊ ስለመሆኑ አንዳች ጥርጥር አልነበረኝም። ሶማሌያውያን መርከብ ሲጠልፉ ጸሃዩ መንግስታችን ደግሞ የስልክ ፓይረት መሆኑን ሂዩማን ራይትስ ዎች በዚያን ሰሞን ነግሮን ነበርና።

Thursday, April 17, 2014

ሰማያዊ ፓርቲ በፌደራል መንግስቱና በቡለን ወረዳ የመሰረተው ክስ ሀሙስ ፍርድ ቤት ይቀርባል!

April 17, 2014
ሰማያዊ ፓርቲ በቤንሻንጉል ጉምዝ በህገ ወጥ መንገድ የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ወደ ቦታቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱና ተገቢው ካሳ እንዲከፈላቸው በተደጋጋሚ ባካሄዳቸው ሰላማዊ ሰልፎችና ባወጣቸው መግለጫዎች የጠየቀ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው ምላሽ ባለመስጠቱ ዜጎቹ የተፈናቀሉበትን ቡለን ወረዳና የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ላይ ክስ መስርቶ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ክሱን ታዋቂው የዓለም አቀፍ የህግ ባለሙያ ዶክተር ያእቆብ ኃይለ ማሪያም ይዘውት የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ቢሮክራሲያዊ ምክንያቶች መዝገብ ሳይከፈትለት እንደቆየ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡Amhara Ethnic group members Ethiopia
ይሁን እንጂ ሰማያዊ ፓርቲ ባደረገው ተደጋጋሚ ግፊት ክሱ በአሁኑ ወቅት መዝገብ ተከፍቶለት፣ የዳኝነት ክፍያ ተከፍሎ በቀጣይ ሀሙስ ሚያዝያ 9/2006ዓ/ም ክሱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስምንተኛ ፍትሃብሄር ችሎት ላይ መታየት እንደሚጀምር ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በጉዳዩ ላይ አቋም ወስዶበት ከሰላማዊ ሰልፉም ባሻገር ዜጎቹ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱና ካሳ እንዲሰጣቸው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ እስካሁንም ድረስ በዜጎች ላይ በሚደርሰው ችግር ከጎናቸው ሆኖ የሞራልና የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡›› ያሉት አቶ ብርሃኑ ፓርቲው ኢትዮጵያውያኑ በመፈናቀሉ ሂደት በደረሰባቸው ችግር ልጆቻቸው የታመሙባቸውን ለህክምና እንዲሁም ለመጓጓዣም ፓርቲው እገዛ ሲያደርግ መቆየቱንና አሁንም ዜጎቹ ፍትህ እስኪያገኙ ድረስ ከጎናቸው እንደሚሆኑ አሳውቀዋል፡፡
በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራታቸው ትክክል ነው ወይ ብለን ላነሳንላቸው ጥያቄ ‹‹አሁንም ማፈናቀሉ ቀጥሏል፡፡ አሁንም ዜጎች እየተፈናቀሉ ስለመሆኑ በተለያዩ ሚዲያዎች ተዘግቧል፡፡ አሁንም ሰልፉን የጠራንበት ምክንያት ይህ የማፈናቀል ህገወጥ ድርጊት ባለመቆሙ ነው፡፡ እኛ እየከሰስን ያለነው ባለፈው የመፈናቀል ህገወጥ ተግባር በተፈጸመባቸው ላይ ነው፡፡ የቡለን ወረዳ ቀኑን ጠቅሶ ‹‹ስለምትፈናቀሉ ልቀቁ!›› ያለበትን ማስታወቂያና ማስጠንቀቂያዎች በመረጃነት ይዘናል፡፡ ይህ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ነው፡፡ ይህን ጥያቄ ማንሳት ደግሞ ዋነኛው ስራችን ነው፡፡›› ብለዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ‹‹አሁን ይህ ድርጊት ከወረዳና ከክልሎች አልፎ የመንግስት ፖሊሲ ወደመሆን በመሸጋገሩ በተደራጀና ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ መታገል አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡›› ብለዋል፡፡ የሰልፉ አላማም በኢህአዴግ የፖሊሲ ችግር ላይ መሆኑን የገለጹት የህዝብ ግንኙነቱ ‹‹ኢህአዴግ መሬት የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ንብረት ነው፡፡›› በሚል ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ተዘዋውረው የመስራትና የመኖር መብታቸውን ስለገደበና በዚህ የተሳሳተ ፖሊሲ ኢትዮጵያ እንደ አገር ትልቅ ችግር እየገጠማት በመሆኑ ችግሩ ከሚደርስባቸው ዜጎች ጎን በመሆንና ሌላውን ህዝብ በማንቀሳቀስ ኢህአዴግ ሃገር የማስተዳደር አቅምም ሆነ ችሎታ እንደሌለው በማጋለጥ ስልጣኑን እንዲለቅ ግፊት ለማድረግ እንደሆነ አቶ ብርሃኑ ለነገረ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል፡፡ የክሱን ሂደትም ሚዲያውያና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲከታተሉት ጥሪ አቅርበዋል፡፡
Source: Negere Ethiopia
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/11866/

Wednesday, April 16, 2014

የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ረዥም ጥቁር ጥላዉን በ(መካከለኛው) አፍሪካ ጥሎአል

April 16, 2014
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የ1994 የሩዋንዳ የጭፍጨፋ እና የእልቂት ጸጸት በ2014 የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ሰማይ ላይ እያንዣበበ ነው!
ባለፈው ሳምንት የሩዋንዳ ህዝብ እርስ በእርስ የተራረደበትን 20ኛውን ዓመት የሩዋንዳ የዘር ፍጅት መጥፎ ገጽታ ለማስታወስ የሀዘን ሳምንት አውጆ ድርጊቱን በመራር ሀዘን ዘክሮታል፡፡ እ.ኤ.አ በኤፕሪል 6/1994 በመንግስት የስልጣን እርከን ላይ የነበሩ አክራሪ የሁቱ ጎሳ አመራሮች፣ የእነርሱ የፖለቲካ አመለካከት ደጋፊዎች እና የተደራጁ ታጣቂ ሚሊሻዎች  ስልታዊ የግድያ ወንጀሎችን በማቀናጀት እና በግንባር ቀደምትነት በመምራት 100 ተከታታይ ቀናት የወሰደ እልቂትን በማደራጀት ከ800 ሺ በላይ ሰላማዊ ህዝቦች በተለይም የቱትሲ እና አክራሪ ያልሆኑ የሁቱ ጎሳ አባላትን ፈጅተዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ1994 ሩዋንዳ 5.5 ሚሊዮን ህዝብ የነበራት ሲሆን ከዚህ ውስጥ 14 በመቶ የሚሆኑት የቱትሲ ጎሳ አባላት ነበሩ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሩዋንዳ 11.5 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሲሆን ከዚህ ውስጥ የቱትሲ ጎሳ አባላት ህዝብ ብዛት ከ10 በመቶ ያነሰ ነው፡፡
Last week, the people of Rwanda began a solemn week of official mourning
ባለፈው ሳምንት የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ (መአሬ) “የሩዋንዳ አምሳያ” የሆነ ለመናገር የሚዘገንን አስፈሪ ቅዠታቸውን መጋፈጥ ቀጥለዋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሀፊ ባንኪሙን በመአሬ እየተካሄደ ባለው “የዘር-ኃይማኖታዊ የማጽዳት” ዕኩይ ድርጊት ላይ ልባቸው በሀዘን የተሰበረ መሆኑን በመግለጽ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፈዋል፣ “የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ከ20 ዓመታት በፊት በሩዋንዳ ህዝብ ላይ የደረሰውን ዕልቂት በግዴለሽነት ከዳር ቆሞ ሲመለከት ነበር… እናም አሁን ደግሞ ለመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ ህዝቦች ህይወት ደህንነት በቂ የሆነ ምንም ነገር ባለማድረግ በከፍተኛ አደጋ ውስጥ ወድቀን እንገኛለን… ለአንዳንድ ሰዎች ይህ ጉዳይ የተረሳ ታላቅ አደጋ ነው፡፡ እኔ እዚህ ያለሁት የዓለም ህዝብ ጉዳዩን እንዳይረሳው ለማሳሰብ እና ለማገዝ ነው… እናም በአሁኑ ጊዜ ለመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ ደህንነት በቂ የሆኑ ተግባራትን ባለማከናወን በትልቅ አደጋ ውስጥ ወድቀን እንገኛለን…በዚህች አገር የዘፈቀደ የጅምላ ግድያ ወንጀሎች በመፈጸም ላይ ይገኛሉ፡፡ የዘር-ኃይማኖት የማጽዳት ዘመቻ እውን በመሆን ላይ ይገኛል፡፡ አናሳዎቹ የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት አገራቸውን ጥለው በመሰደድ ላይ ናቸው፡፡ እንዲህ ያለ ድርጊት ‘በፍጹም እንደገና አይደረግም’ እያልን እራሳችንን እያታለልን መቀጠል የለብንም፡፡ ይህንን አዘናጊ አባባል ብዙ ጊዜ ደግመን ደጋግመን ብለነዋል፡፡ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ ተገቢውን እርምጃ መውሰድ እና በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ እየተፈጸመ ያለውን የጅምላ ፍጅት በአስቸኳይ ማስቆም ይኖርብናል…“ በማለት ሀሳባቸውን አጠቃለዋል፡፡
ከ20 ዓመታት በፊት የሁቱ የዘር ግንድ የሆኑት የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ጁቬናል ሀብያሪማና ተሳፍረውበት የነበረው አውሮፕላን በተተኮሰ መሳሪያ ከተመታ በኋላ ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል፡፡ እ.ኤ.አ በ1993 የሁቱ እና የቱትሲ ጎሳ አባላት በጋራ የጥምር መንግስት ለማቋቋም የተጀመረውን ጥረት ወደ ጎን በማለት እና አክራሪ የሁቱ ጎሳ አባላት ቀደም ሲል በሁለቱ የጎሳ አባላት መካከል ተደርጎ የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ የቱትሲ ጎሳ አባላትን እነርሱ በረሮዎች እያሉ በሚጠሯቸው የቱትሲ የጎሳ አባላት ላይ እልቂት በመፈጸም “የመጨረሻውን ጦርነት” ወደ ተግባር አሸጋገሩት፡፡ አካዙ (የሁቱ ጎሳ አባላት የፖለቲካ አመራሮች እና ልሂቃን) እየተባሉ የሚጠሩት የጅምላ ዘር ፍጅቱ ከመጀመሩ ቢያንስ ከአንድ ዓመት በፊት የቱትሲ ጎሳ አባላት የሆኑትን ሩዋንዳውያን/ት ዜጎችን ለመፍጀት የታሰበበት ዕቅድ ነደፉ፡፡ የእራሳቸውን ሬዲዮ ጣቢያ (ኮሊንስ) አቋቋሙ፡፡ እ.ኤ.አ በኤፕሪል 1994 የዘር ማጥፋት ፍጅቱ በተጀመረበት ወቅት እነዚህ የሁቱ የፖለቲካ አመራሮች ሬዲዮ ጣቢያቸውን ነፍሰ ገዳዮችን ለማደፋፈር እና ለማበረታታት ይጠቀሙበት ነበር፡፡ ግድያ እንዲፈጸምባቸው ያዘጋጇቸውን የቱትሲ ጎሳ አባላት ስም ዝርዝር የሚያነቡበት እና እነዚያን ዘግናኝ የዘር ፍጅት ወንጀሎች እንዲፈጽሙ ለሚታዘዙ ገዳይ ሚሊሻዎች (ኢንተርሀሞይ እና ኢምፑዛሙጋምቢ) የትዕዛዝ መልዕክቶች የሚተላለፉበት ነበር፡፡ ሁቱዎቹ በተደጋጋሚ በሬዲዮ ጣቢያው እንዲህ የሚል መልዕክት ያስተላልፉበት ነበር፣ “በእውነት ሁሉም የቱትሲ ጎሳ አባላት ከምድረ ገጽ መጥፋት አለባቸው፣ ቱትሲዎች ከዚህች አገር መጥፋት አለባቸው… ቱትሲዎችን እያነጣጠረ ለሚመታው መሳሪያ ምስጋና ይግባውና ቱትሲዎች ቀስ በቀስ በመጥፋት ላይ መገኘታቸው ብቻ አይደለም ዋናው ጉዳይ ሆኖም ግን እንደ አይጥ እየታደኑ መገደላቸው ጭምር እንጅ፡፡” እ.ኤ.አ በ1994 ከሩዋንዳ ከተማ ኪጋሊ በ30 ማይል ርቀት ላይ ከምትገኘው እና በሩዋንዳ ታላቅ ከተማ ከሆነችው ኒያማታ በምትባለው ከተማ የሚኖሩ 120 ሺ የሩዋንዳ ዜጎቸ ነበሩ፡፡ በአንድ ወር እና በአንድ ወር ከግማሽ ጊዜ ውስጥ በዚህች ከተማ ውስጥ 50 ሺ ብቻ ሰዎች ቀሩ፡፡ ከስድስት ቱትሲዎች መካከል አምስቱ ይገደሉ ነበር፡፡”
በአሁኑ ጊዜ የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ (መአሬ) በኃማኖት ጽንፈኝነት፣ በጅምላ ጥላቻ እና በእርስ በእርስ ጦርነት ማጥ ውስጥ ተዘፍቃ ተበታትና ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ በ2013 ሰለቃ ሚሊሻ (እ.ኤ.አ በማርች 2013 የመአሬን መንግስት በኃይል ያስወገዱት የአማጽያን ህብረት ቡድኖች) “በአገሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ እና በመላ አገሪቷ የጭካኔ ግድያዎችን ማድረግ ጀመሩ፣ እናም የአገሪቱን ዋና ከተማ ባንጉይን በመቆጣጠር የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ፍራንኮይስ ቦዚዝን ከስልጣን አባረሩ፡፡ በቀጣዮቹ አስር ወራት የሰለቃ ኃይሎች ለቁጥር የሚያታክቱ ሰላማዊ ህዝቦችን ፈጁ፣ ብዙ መንደሮችን በእሳት አጋዩ እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶችን ዘረፉ፡፡ “ከስልጣን የተወገዱትን ፕሬዚዳንት ቦዚዝን ጨምሮ 90 በመቶ የሚሆነው የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ ህዝብ የክርስትና እምነት ተከታይ ቢሆንም ቅሉ አብዛኞቹ የሰለቃ ኃይሎች እና መሪያቸው ሚሸል ጆቶዲያ የእስልምና ኃይማኖት እምነት ተከታዮች ናቸው፡፡ እንደ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዘገባ ከሆነ የሰለቃ አማጽያን የበቀል ጥላቻ ባላቸው የክርስትና እምነት ተከታይ በሆኑት እና ምንም ዓይነት የጦር መሳሪያ ለምሳሌም ያህል ጎራዴ ባልታጠቁት እንዲሁም ባልተጠናከረ መልክ በተደራጁት በሳንጎ በሚኖሩት ጸረ ባልካ ተዋጊዎች ላይ ተኩስ በመክፈት ፈጣን የሆነ የማጥቃት እርምጃ ወሰዱባቸው፡፡ እ.ኡ.አ በ2013 የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ውስጥ የጸረ ባልካ ተዋጊ ኃይሎች በሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላት ላይ በተለይም በመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ ሰሜናዊ ምስራቅ በሚኖሩት ዜጎች ላይ ዘግናኝ የሆነ የጥቃት እርምጃ ወስደውባቸዋል፡፡ ጥቃቱ በተጠናከረ መልኩ የቀጠለ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሰላም አስከባሪ ኃይል በምዕራብ የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ የሚኖሩ የሲቪል የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት ላይ እየተካሄደ ያለውን የዘር ማጽዳት ዘመቻ ማስቆም አልቻለም፡፡ ከሩዋንዳ ዋና ከተማ ከባንጉይ በ150 ማይል ርቀት ላይ በምትገኘው ያሎኬ በምትባል ከተማ ከአንድ ዓመት በፊት ወደ 30 ሺ የሚገመቱ የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት በስምንት መስጊዶች አማካይነት እምነታቸውን እያራመዱ በሰላም እና በፍቅር ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ግን እንደ ሂዩማን ራይትስ ዎች እማኝነት ከሆነ በአሁኑ ጊዜ ከ500 ያነሱ የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት እና አንድ መስጊድ ብቻ ቀርተዋል፡፡
ባለፈው ዓመት የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በመካከለኛው አፍሪካ ሬፑብሊክ እየተካሄደ ያለውን የዘር-ኃይማኖት የማጽዳት አደገኛ ዘመቻ በማስመልከት የመጀመሪያ የማስጠንቀቂያ ደዎል አሰምተው ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በ2013 አምነስቲ ኢንተርናሽናል በመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ በመካሄድ ላይ ያለው “የሰብአዊ መብት ቀውስ ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን የሚገልጽ ሪፖርት በማውጣት ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ” ነበር፡፡ የኃይል እርምጃው እና እልቂቱ እየጨመረ በመጣ ጊዜ ብዙ ሺ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች (2 ሺ የፈረንሳይ ወታደሮች እና ወደ 6 ሺ የሚጠጉ የአፍሪካ ህብረት ወታደሮች) ወደ መካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ ተልከዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት የተባበሩት መንግስታት 12 ሺ የሰላም አስከባሪ ኃይል እንዲሰማራ ትዕዛዝ አስተላልፎ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ተመደበ የተባለው የሰላም አስከባሪ ኃይል እ.ኤ.አ እስከ ሴፕቴምበር 2014 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ በቦታው አልደረሰም፡፡ ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት “በመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ ላይ ገደቡን ባለፈ መልኩ እየተካሄደ ያለው የኃይል እርምጃ ሁነኛ ገደብ ካልተበጀለት በስተቀር በጠቅላላው በአገሪቱ ውስጥ የሚኖሩት ማህበረሰቦች በሙሉ አገሪቱን ጥለው ለመሰደድ ይገደዳሉ” የሚል ጠንካራ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የጉዳዩን አሳሳቢነት በውል አመላክቷል፡፡ በዚህ የሰው ልጅ እልቂት የአካሄድ ፍጥነት መጠን ከተሰላ እና የዘር ማጽዳት የኃይል እርምጃ ዘመቻው ዒላማ በዚሁ ፍጥነት የሚቀጥል ከሆነ በአብዛኛው የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ ምንም ዓይነት የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት የሚባል ነገር ሊገኝ አይችልም፡፡” በማለት ስጋታቸውን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሳውቀዋል፡፡
የሩዋንዳን የ1994 እና የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ የ2014 ሁኔታ በጎንዮሽ በንጽጽር ሲታይ አስደንጋጭ ሁኔታ ነው፡፡ እ.ኤ.አ የ1994 ሩዋንዳን ሁኔታ ስንመለከት የአፍሪካ ህብረት እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዩናይትድ ስቴትስን እና የተባበሩት መንግስታትን ጨምሮ ከቁጥጥር ውጭ ወጥቶ ለነበረው የዘር ማጽዳት እልቂት እና ፍጅት ጆሮ ዳባ ልበስ የሚል ምላሽ ነበር የሰጡት፡፡ እ.ኤ.አ የ2014 የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ ሁኔታ ሲገመገም ደግሞ “በዘር-ኃይማኖት ማጽዳት” ዕኩይ ምግባር ምክንያት በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ዜጎች ሲጨፈጨፉ እና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ከቀያቸው ሲፈናቀሉ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የይስሙላ የሰላም አስከባሪ ኃይል በመመደብ የታዕይታ ስራ ለማሳየት ከመሞከር ባለፈ የንጹኃን ዘጎችን ህይወት ለመታደግ የሚያስችል ተጨባጭነት ያለው ስራ ሲሰራ አልታየም፡፡ ለድፍን ሙሉ ዓመት በመካለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ በግልጽ ሊታይ የሚችል ጥላቻ እና አደጋውንም መከላከል የሚያስችል ዕድል የነበረ ቢሆንም የአፍሪካ ህብረት እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አጋጣሚውን በበጎ መልኩ ሳይጠቀምበት ባክኖ ቀርቷል፡፡ አምነስቲ ኢንተርናሽናል እንዲህ የሚል ማሳሰቢያ ሰጥቷል፣ “ለ10 ወራት በስልጣን መንበር ላይ በመቆየት  ለደረሰው ዕልቂት፣ ከህግ አግባብ ውጭ ለተፈጸሙ ግድያዎች፣ ለአስገድዶ መድፈር፣ ማሰቃየት እና ዝርፊያ እንዲሁም በገፍ ለክርስቲያን መንደሮች በእሳት መጋየት እና መውደም ሰለቃዎች ተጠያቂዎች ናቸው፡፡ ሰለቃዎች ጥቃታቸውን ከሰነዘሩ በኋላ ወደ ኋላ ሲያፈገፍጉ ዓለም አቀፉ ኃይል ለጸረ ባልካ ታጣቂዎች ድጋፉን በመስጠት ከተማ በከተማ ላይ እየተቆጣጠሩ ኃይላቸውን እንዲያጠናክሩ አጋጣሚውን ፈጥሮላቸዋል፡፡ የተከሰተው የኃይል እርምጃ እና የሙስሊም ማህበረሰብ አባላትን የማፈናቀሉ ሁኔታ የሚጠበቅ ክስተት ነበር፡፡“

Tuesday, April 15, 2014

አንድ ባርያ ነጻ የሚወጣው መቼ ነው? ሲፈቅድ ነው? ወይስ ሲፈቀድለት? (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

April 14, 2014
በአለፈው ሳምንት (ፋክት ቁጥር 36) ወይዘሮ መስከረም የተለያዩ መጻሕፍትን በመጥቀስ በሴቶች ላይ ያለውን መጥፎ ጫና በደንብ ያስመሰከረች ይመስለኛል፤ ግን እኮ በሴቶች ላይ ያለው ጫና የቆየ፣ ክፉና ጎጂ መሆኑን ማንም ያውቀዋል፤ ቁም-ነገሩ ያለው ከዚያ የባህል ጭነት በራስ ጥረት ወጥቶ፣ ነቀፌታንም ሆነ እርማትን ለመቀበል ሳይፈሩና ሳያፍሩ እንደመስከረም በአደባባይ ሀሳብን በመግለጽ በአገርና በወገን ጉዳይ መሳተፍና ሌሎችም እንዲሳተፉ የተቻለን ሁሉ ማድረጉ ላይ ነው፤ ለዚህ ነው ይህንን መልስ የምጽፈው፤ ወይዘሮ መስከረም በአጋጠሟትና በምታያቸው እንቅፋቶች ላይ ማተኮርዋ እንደርስዋ መንፈሳዊ ወኔው የሌላቸውን ያስፈራራቸዋል እንጂ አያበረታታቸውም፤ የማንንም አፍአዊ ጫና ተቋቁመው በራሳቸው የውስጥ ኃይል እንዲመሩ እናድርግ።
Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopher
አንድ መጽሐፍን በመጥቀስ ወይዘሮ መስከረም የሚከተለውን ጽፋለች፡–
ፈጣሪ የሠራውን ውጫዊ ገጽታን ማሽሞንሞን በቂ እንደሆነ ሲነገራት የኖረች ሴት፣ በምን ተነሳሺነት አእምሮዋን የሚመግብ እውቀት ልትሻ ትችላለች? … በልጅነት እውቀትን ወደመሻት ያልተገፋ ማንነት በጉብዝና ወራት አላዋቂ በመሆን ቢወቀስ ትርጉም አይኖረውም፤ …››
ወይዘሮ መስከረም ሔዋን ሲነገራት የማትሰማ የመጀመሪያዋ ሰው (ልብ በሉ ሴት አላልሁም፤) መሆንዋን እንዴት እስከዛሬ ሳታውቅ ቀረች? ባለመጽሐፉም ይሁን መስከረም የሔዋንን ታሪክ ሳያነሡ መቅረታቸው መሠረታዊ ስሕተት ነው፤ በተጠቀሱት ሁለት ዓረፍተ ነገሮች ውስጥ አንድም እውነትን የሚመስል ነገር የለም፤ መስከረም‹‹የሔዋን ዘር›› ከማለት በፊት የሔዋንን ሥራ ቆም ብላ ብታስታውስ የጠቀሰችውን መጽሐፍ እኔ እንደምነቅፈው ትነቅፈው ነበር፤ የሔዋን ታሪክ የሚነግረን የሚከተለውን ነው፡ ‹‹ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደሆነ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፣ ለጥበብም መልካም እንደሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው፤ እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ፤ የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ፤›› ዘፍ. 3
የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ ማለት ‹‹እንደእግዚአብሔር መልካምንና ክፉን የሚያውቁ›› ሆኑ ማለት ነው፤ አሁንም ሔዋን መስከረምና ባለመጽሐፉ እንዳቀለሏት አለመሆንዋን መረዳት ይቻል ነበር፤ እንዲያውም ከዚህ በፊት እንደጻፍሁት ሔዋን የመጀመሪያዋ አብዮተኛና የነጻነት እናት ነች ለማለት ይቻላል! በአንጻሩ አዳም የፍርሃት አባት ነው፤ ‹‹ራቁቴን ስለሆንሁ ፈራሁ፤›› ያለው እሱ ነው! ስለዚህ ወይዘሮ መስከረም ‹‹የሔዋን ዘር›› የምትለውን በድላለችና ይቅርታ መጠየቅ ሳያስፈልጋት አይቀርም!
ሔዋን የተጠቀመችው ውጫዊ ገጽታን የሚያሽሞነሙን ሳይሆን የውስጥን የመንፈስ ኃይል ቆፍሮ በማውጣት ነበር፤ በዚህ የውስጥ ኃይል ለሚጠቀም ከውጭ ግፊት አይጠብቅም።
‹‹እውቀትን ወደመሻት ያልተገፋ ማንነት›› አይወቀስም፤ ትላለች ወይዘሮ መስከረም፤ እየተገፉ የሚገኘው ባርነት ነው፤ እውቀት የሚገኘው በነጻነት ነው፤ መገፋት ከእውቀት ያርቃል እንጂ ወደእውቀት አያስቀርብም፤ የመስከረም ዋናው መልእክት ሰላቢውን እንጂ ሰለባውን አትውቀስ የሚል ነው፣ ወይም የኔ ሀሳብ አህያውን ፈርቶ ዳውላውን ዓይነት ሆኖባታል፤ ለመሆኑ ሰለባ የሚሆን ከሌለ ሰላቢ ይኖራል ወይ? ሰለባ ከመሆን በፊት ሰለባ ላለመሆን መጣር አንዱ የኑሮ ዓላማ አይሆንም ወይ? ከዚህ በፊት ስለጨቋኝና ተጨቋኝ ደጋግሜ ጽፌ ነበር፤ ጭቆና የጨቋኙ ባሕርይ የሚሆነውን ያህል የተጨቋኙም ባሕርይ ይሆናል፤ ለጨቋኙ ጭቆና የሚጠቅመውን ያህል ለተጨቋኙም ጭቆና ይጠቅመዋል፤ ለጨቋኙ ጭቆና የኑሮው መሠረት የሆነውን ያህል ለሚርመሰመሱት የጨቋኝ ሎሌዎች ጭቆና የኑሮ መሠረታቸው ነው፤ እንዲህ እያለ ወርዶ ወርዶ የጭቆና ጠቃሚነት ለሎሌው ሎሌ፣ ለሎሌው ሎሌ ሎሌ … በኢትዮጵያ ምናልባትም የመጨረሻዋ የጭቆና ሰለባ ሚስት ትሆናለች፤ ወይም ልጆች ይሆናሉ! ጨቋኝና ተጨቋኝ የባሕርይ ቁርኝት አላቸው፤ አንዱ ያላንዱ አይኖርም፤ ወይዘሮ መስከረም ይህ እውነት ያልሆነበት ሁኔታ ወይም አጋጣሚ የምታውቀው ካለ ብታጋራን ደስ ይለኛል፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹ሙታናቸውንም እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፤›› የሚለው ኢየሱስ ክርስቶስ የሞቱትንና በቁማቸው የሞቱትን ሲያመሳስላቸው ነው! ለእኔ የሚታየኝ እንዲህ ነው።
መስከረም ብዙ ታላላቅ ሴቶችን ጠቅሳለች፤ በእስዋ ግምት ሁሉም በአባታቸው ወይም በባላቸው እየተገፉ ወደትልቅነት መድረኩ የወጡ ናቸው፤ አዙራ ብታየው የጠቀሰቻቸውን ሴቶች ገፉ የምትላቸው ወንዶች መጀመሪያውኑ በሴቶቹ ተገፍተው እንደነበረስ ሊታሰብ አይገባም? ምናልባት ከጠቀሰቻቸው ሴቶች ይልቅ መስከረም የሄለን ኬለርን ታሪክ ብታስታውስ ኖሮ መገፋትን አታነሣም ነበር፤ ሄለን ኬለር በሕጻንነትዋ ዓይኖችዋም ጆሮዎችዋም ሥራቸውን አቆሙ፤ የሄለን ኬለር የመንፈስ ጥንካሬ ከውስጥዋ አዲስና የተሻሉ ዓይኖችንና ጆሮዎችን እንድታበቅልና እንድትማር፣ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲም የመጀመሪያዋ ሴት ምሩቅ ለመሆን እንድትበቃ አድርጓታል፤ ይህች አስደናቂ ሴት ከመቶ ሠላሳ ዓመታት ግድም በፊት ማኅበረሰቡ በሴቶች ላይ የነበረውን አጥር ሰብራ፣ ዓይኖችዋ ባለማየታቸውና ጆሮዎችዋ ባለመስማታቸው የገጠማትን እክል አሸንፋ ራስዋን ከወንዶች በላይ ለማድረግ በቅታለች።
መገፋትን የሚፈልግ ሁሉ፣ ካልገፉት የማይነቃነቅ ሁሉ፣ ሬትን ሲግቱት ይጣፍጣል እያለ የተቀበለ ሁሉ፣ ዶሮ ማታ፣ ዶሮ ማታ፣ እያሉ አታልለው እንኳን ዶሮ የለም ሹሮ ሲሉት የማይናደድ ሁሉ፣ ምኞቱ ልደግ ልመንደግ እያለ ሲነዘንዘው በአፈና ጭጭ የሚል ሁሉ ለወቀሳ ብቻ አይደለም ለውርደትም ክፍት ነው፤ ስለዚህም ተወቅሶ ከውርደት ከዳነ ወቀሳው ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል ማለት ነው፤ ዞሮ ዞሮ የሰው ልጆች ሁሉ — ሴት፣ ወንድ፣ ወጣት ሽማግሌ-አሮጊት፣ ባለሥልጣን ተራ፣ ገበሬ ነጋዴ፣ ወታደር ፖሊስ፣ አስተማሪ አስተዳዳሪ፣ ዳኛ ጠበቃ፣ ሀኪም መሀንዲስ፣ … — የፈለገውን ቢሆን ላለበት ሁኔታ ኃላፊነቱ የራሱና የግሉ ነው፤ ራሱን የሚገነባው ወይም ራሱን የሚንደው ራሱ ነው፤ ሰበብ እየፈለጉ ከዚህ ኃላፊነት መውጣት ቀላል ቢመስልም ተመልሶ እምቦጭ ነው፤ ዳገቱን ለመውጣት የሚመረውን እውነት መቀበል ያሻል።
በመጨረሻም በማናቸውም መንገድ፣ በማናቸውም ጊዜ፣ በየትኛውም ቦታ ወደቁልቁለት የሚገፉትን ወይም የሚነዱትን ‹‹እምቢ!›› ብሎ ድምጹን ያላሰማ ገደል ገብቶ ሲንፈራፈር ከራሱ በቀር የሚወቅሰው የለም፤ አቅመ-ቢስነት ከውጭ አይመጣም።
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/11818/

የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ሚና በተመለከተ በኖርዌይ ኦስሎ ሕዝባዊ ውይይት ተካሄደ

April 14, 2014
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
Ginbot7 meeting in Norway
በዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ  የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት አፕሪል ቅዳሜ 12/2014  በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ  የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ተሳትፎ በተመለከተ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ተካሄደ:: በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ የሚጠጉ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች ከኦስሎ እና ከተለያየ ከተማ በመምጣት በስብሰባው ላይ የተገኙ ሲሆን  የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ በመሆን ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል::
ሕዝባዊ ስብሠባው በኖሬጅያውያን የሰአተ አቆጣጠር ከቀኑ 15:00 እስከ ምሽቱ 21:00 ሰዓት የተካሄደ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አቢ አማረ በኢትዮጵያ ውስጥ በወያኔ አረመናዊ ስርአት በጭካኔ በግፍ ለተገደሉ እና በተለያዩ አስር ቤቶች በፖለቲካ ኣስተሳስባችው ምክንያት ያለወንጀላች የሚስቃዩ ውድ ኢትዮጵያዊን ወገኖቻችን በማስብ  በዚሁ ዘረኛ ቡድን አስቃቂ የኣካል ጉዳት ለተፈጸባቸው ኢትዮጵያዊን  የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት በማስደረግ ስብሰባውን አስጀምረውታል::
በመቀጠለም አቶ ዮሀንስ አለሙ የዴምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሊቀመንበር የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸው ስለ ዲምክራሲያዌ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አመሰራረት እና ስለ ድጋፍ ድርጅቱ አላማ በማብራራት የድጋፍ ድርጅቱ በአሁኑ ሰአት በሀገር ቤት በሰላማዊ ትግል የወያኔን መንግስት ለመጣል እየታገሉ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶችን እየረዳ እንደሚገኝ እና ከሀገር ውጭ ደግሞ የወያኔን መንግስት  በሁለገብ ትግል  ለማስወገድ እየሰራ ያለውን የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ የፖለቲካ ድርጅትን በግንባር ቀደምነት እየረዳ እንዳለ በመግለጽ  የወያኔን ዘረኛ ስርአት ለመጣል ሁሉም ሰው አስተዋጿ ማድረግ እንደሚጠበቅበት እና ማንኛውም  ኢትዮጵያዌ ዜጋ በሀገራችን የጋራ ጉዳይ ስለሆነው  የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ሀሳብ በመለዋወጥ ፣በመካከላችን ያሉትን ማንኛውንም የሃሳብ ልዩነቶች ወደ ኋላ በመጣል ፣ በመቻቻል፣ ሀገር እያፈረሰ እና ሕዝብ እያዋረደ ያለውን የዘረኛውን የወያኔን መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሁለገብ ትግል ለማስወገድ መረባረብ እንዳለበት አጽኖት ሰጥተው ንግግር አድርገዋል::
Ethiopians public meeting in Norway
በመቀጠለም ዲምክራሲያዊ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ድጋፍ ከሚሰጣቸው ድርጅቶች መካከል አንዱ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል የሆኑት አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ ሰፊውን ጊዜ በመውሰድ ከንጉሱ ስርአት ጀምሮ በደርግ መንግስት ዘመንም በሀገራችን የተደረጉ የፖለቲካ ንቅናቄዎችንና ለውጦችን አንድ በአንድ በመዘርዘር አሁን ካለው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ጋር በማነጻጸር ሰፋ ያለ ትንታኔ ያቀረቡ ሲሆን አሁን ላይ ሀገሪቱን እየመራው ነው የሚለው የወያኔ መንግስት ከዚህ ቀድሞ ኢትዮጵያን ከመሩት ከሁለቱ መንግስታቶች ማለትም ከንጉሱም ከደርግም መንግስት ጋር ሲነጻጸር ፈጽሞ እንደማይገናኝ የወያኔ መንግስት ዘረኛና የዘረኝነት ፖለቲካ እያራመደ ያለ አረመናዊ መንግስት እንደሆነ አብራርተዋል::
የግንቦት 7  የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ አክለውም ከወያኔ በፊት የነበሩ ሁለቱ መንግስታቶች ለውድቀት የዳረጓቸውን ምክንያቶች በመጥቀስ የወያኔን አንባ ገነናዊ መንግስት ለአፋጣኝ ውድቀት ሊዳርጉት ይችላሉ የሚሉትን ግልጽ ምክንያቶች በመዘርዘር አስቀምጠዋል:: አቶ ቡዙነህ በሁለት የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በማንሳት እና በማብራራ ከሕዝብ ውይይት እንዲያደርጉበት ለመወያያ ያቀረቡ ሲሆን እነዚህም:
1, በሙስሊሙ ማህበረሰብ እና በወያኔ መካከል ያለው ግጭት
2, የህዳሴ ግድብን  በማስመልከት ያለው ተቃውሞ
ስለሙስሊሙ ማህበረሰብ ተቃውሞ ሲናገሩ የሙስሊሙ ትግል በሁለት አመታት ውስጥ የተደረገው ሰላማዊ ትግል በጣም የተሳካና ወያኔ በቀላሉ ሊያዳፍነው ያልቻለው ሰላማዊ መብትን የመጠየቅ ትግል እንደሚያደንቁ በመናገር ነገር ይህ በሙስሊም ማህበረሰብ በኩል እየተደረገ ያለው ትግል እስከ አሁን ድረስ ከመንግስት በኩል ምንም አይነት መልስ ሊያገኝ እንዳልቻለ እና ወደፊትም ከወያኔ መንግስት በኩል ምንም አይነት መልስ ያገኛል የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል:: ለዚህም ማስረጃው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ከጠየቋቸው አራት የመብት ጥያቄዎች አንዱም ካለመመለሱ በተጨማሪ እስካሁን መሪዎቻቸውም በሃሰት ውንጀላ በእስር እየማቀቁ ያለፍርድ እየተንገላቱ መሆናቸው ነው::
ነገር ገን አሁን እየሆነው ባለው ሁኔታ በእንደዚህ አይነት መንገድ እስከመቼ ድረስ የሙስሌሙ ትግል ይቀጥላል በማለት የተናገሩ ሲሆን አሁን እየሄደ ባለው አካሄድ የሙስሊሙ ተቃውሞ የትግል አቅጣጫውን እስካልቀየረ ድረስ ረጅም ርቀትን ትግሉ ሊቀጥል ይችላል የሚል እምነት እንደሌላቸው እና ነግር ግን የሙስሊሙ ጥያቄ ከእምነት መብት ጥያቄ ባሻገር ወደ የዜግነትን መብት ወደ ማስከበር መለወጥና መሸጋገር  እናደለበት በመናገር የሙስሊሙ ማእበረሰብ ጥያቄ ፍሬ ሊያፈራ የሚችለው  ትግሉ በዚህ መልኩ ሲቀጥል እንደሆነ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰተዋል::
በሁለተኛም የህዳሴ ግድብ በሚመለከት  ያቀረቡት ሀሳብ ወያኔ የራሱን የፖለቲካ ኪሳራና በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለዉን ግፍ በዕድገት ስም ለመሸፈን ያመጣዉ እንጂ ታቅዶበትና ለህዝቡ በማሰብ እንዳልሆነ በኢትዮጵያና በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለዉ ግፍ እንደ ማስረጃነት በማቅረብ ያብራሩ ሲሆን እንደ ምሳሌም ወያኔ ሃገራዊ የሆነ አላማ ይዞ ካለመነሳቱ አንፃር የሃገርን ድንበር አሳልፎ እስከመስጠት እየሄደ ያለበትን ሁኔታ ጠቅሰው ይህ አሰራር ደግሞ የዲክታተሮች ባህሪ እንደሆነ አብራርተዋል::
የወያኔ መንግስት በህዳሴ ግድብ ሰበብ ምክንያት በማድረግ በመላው አለም ኢትዮጵያኖች በሚኖሩበት ሀገሮች በመዞር የዲያስፖራውን ቀልብ ለመውሰድ የሚያደርገው የአባይ ቦንድ ሽያጭ ሩጫ በዲያስፖራ ተቃዋሚዎች አማካኝነት በፍጹም እንዳልተሳካለት ይህንንም የወያኔ በአባይ ቦንድ ሽያጭ ስም ገንዘብ ዘረፋ በመቃወም ወያኔን አሳፍረው ከመለሱት መካከል በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች እንደሆኑ በማስታወስ  የዚህ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሰበብ የወያኔን መንግስት ወደ መጥፎ ውድቀት ላይ ሊጥለው እንደሚችል በማመን የወያኔ መንግስት በአሁን ሰአት ከግብጽ መንግስት ጋር እየገባ ያለው ሰጣ ገባ ለኢትዮጵያ መጥፎ ሊሆን እንደሚችል በመግለጽ ንግግራቸውን አጠቃለዋል::
በመቀጠልም አቶ ብዙነህ ባነሷቸው ነጥቦችና እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ከስብሰባው ተሳታፊዎች ለቀረበላቸው በርካታ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጓል፥፥ ከውይይቱም በማስቀጠል የዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ዳንሄል አበበ የዲምክራሲያዌ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የአቋም መግለጫ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ድርጅታቸው ወያኔ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍና በደል ፈጽመው እንደሚያወግዙ እና ዴምክራሲያዌ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሁል ጊዜ ከግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ ጎን እንደሚቆም ቃል በመግባት የአቶ ቡዙነህ ፅጌን በኖርዌይ በመገኛት ለህዝቡ ለሰጡት ገለጻ አመስግነዋል::
በዝግጅቱ መጀመሪያና ማጠቃለያ ላይ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል መዝሙር በመዘምራን የተዘመረ ሲሆን በየጣልቃው የተለያዩ የባህል ዘፈኖች በተወዛዋዦች ታጅቦ የቀረበ ሲሆን ጣእም ያለው ባህላዊ ምግብም በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የሴቶች ክፍል ተስተናግዷል፥፥ ስብሰባውን ተጀምሮ እስኪያልቅ አቶ ፍቅሬ አሰፋ መርተውታል::
በመጨረሻም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ለዝግጅቱ መሳካት የበኩላችሁን ላበረከታችሁና ከተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች ረዥም ርቀት በመጓዝ የዝግጅቱ ታዳሚ ለነበራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን እና እንዲሁም የድርጅቱ አባላቶች ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን::
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/11826/

Sunday, April 13, 2014

አሸባሪው ኢህአዴግና ነፃው ፕሬስ

April 11, 2014
ከሚልክያስ መንግስቱ
በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ መንግስት ሀገሪቱን ተቆጣጥሮ ስልጣን ከያዘ 23ዓመት አስቆጠረ። ይህን ያህል አመት በስልጣን ቆይቶ ህዝቡን በሰላም መምራት አልቻለም። ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ህዝብ ነፃ አውጥቻለሁ፣ ሀገሪቱንም እያሳደኩ ነው..ቢልም ህዝቡ ግን፥ ኑሮ ተወደደ፣ ሀገራችን ተከፋፈለች፣ ዲሞክራሲ የለም፣ ሰብአዊ የመብት ረገጣ እየተፈጸመ ነው በማለት ማማረሩን ቀጥሎዋል። ከብዙ ኢትዮጵያውያኖች ጋር በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ ገብቶዋል።
ህዝቡ በመንግስት ላይ ያለውን ጥያቄና ቅራኔ በማሳወቅ ዙሪያ ነፃው ፕሬስ ታሪካዊና አገራዊ ግዴታውን በጀግንነት እየተወጣ ነው። በዚህም ምክንያት የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞች የአንባገነኑ ኢህአዴግ መንግስት ሰለባ ሆነዋል። እንደ አምንስቲ መግለጫ መሰረት ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘበት ከ1984ዓ.ም ጀምሮ ከ200 በላይ ጋዜጠኞች ተሰደዋል። ከ1992 እስከ 2005 ብቻ 38 ጋዜጠኞች እንደታሰሩ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች የሆነው ሲ.ፒ.ጄ ገልጾዋል። ሲ.ፒ.ጄ ባወጣው መግለጫ ባለፉት 10 አመታት ከ79 በላይ ጋዜጠኞች ሲሰደዱ ከ75 በላይ የሚሆኑ አሳታሚ ድርጅቶች እንደተዘጉ ገልጾዋል። መንግስትን በድፍረት በመተቸታቸውና እውነትን ለህዝብ በማሳወቃቸው ምክንያት በዋነኛነት ከሚታወቁት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ርእዮት አለሙና ውብሸት ታዬ እስከአሁን በእስር ይሰቃያሉ።
የኢህአዴግ መንግስት ከፈፀማቸው ፋሺስታዊ ድርጊቶች መካከል ታሪክ ይቅር ከማይላቸው የሚከተሉት ይጠቀሳሉ። አንጋፋውና እውቁ ጋዜጠኛ ሙልጌታ ሉሌ አራት ጊዜ በማሰር 16 ክስ መስርተውበታል። ይህም አልበቃ ብሎ የወያኔ ደህንነቶች በመኪና ገጭተው አደጋ አድርሰውበታል። ቢሮውን አቃጥለውበታል። እዚህ አሜሪካ ሀገር ከመጣ በኋላ ፓስፖርቱን ለማሳደስ ሲጠይቅ ፖስፖርቱን እንዲቀማ አድርገዋል። የተለያዩ ጋዜጦች አሳታሚ የነበረው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በማእከላዊ ተደብድቦዋል። ባለቤቱ ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል እስር ቤት ወልዳለች። አሸባሪው ወያኔ/ኢህአዴግ በእስክንድር ላይ በፈጠራ ክስ 18 አመት ፈርዶበታል። የነፃው ፕሬስ አባል የነበረው ጋዜጠኛ መኮንን በወያኔ ደህንነቶች በተፈፀመብት እስርና እንግልት ምክንያት የገዛ ህይወቱን አጥፍቶዋል። የሕወሐት/ኢህአዴግን ምስጢር በድፍረት ሲያጋልጥ የነበረውና ኢየሩሳሌም አርአያ በሚል ብእር ስም የሚታወቀው ጋዜጠኛ አርአያ ተስፋማርያም በሰባት ፌዴራል ፖሊሶች ተደብድቦ ስድስት ሜትር ድልድይ ውስጥ ተወርውሮዋል፤ አካሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል። ባለፈው ሳምንት ደግሞ የአሜሪካ ድምፅ ባልደረባ የሆነው አንጋፋው ጋዜጠኛ ሰሎሞን ክፍሌ የሚወዳት ባለቤቱን በሞት ማጣቱን ተከትሎ አስክሬንዋን ይዞ አገር ቤት መሄድና አፈር ማልበስ አልቻለም። አገር ወዳድና ለእውነት የቆመ ጋዜጠኛ በመሆኑ በወያኔ/ኢህአዴግ የውሸት ክስ ስለተለጠፈበት ብቻ የ30 አመት ባለቤቱ የቀብር ስነስርአት ላይ መገኘት አልቻለም። አሸባሪው ኢህአዴግ ዛሬም በጋዜጠኞች ላይ የሚፈፅመው አፈናና እስር ቀጥሎዋል።
Free Ethiopian journalists poster
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/11761/

የኢትዮጵያ መንግስት በረዳት አብራሪ ኃይለመድህን አበራ ላይ ክስ መሰረተ

April 11, 2014
በተመስገን ደሳለኝEthiopian Airlines plane Co-Pilot Hailemedehin Abera Tagegn charged

-ከ253, 336 ከ42 ሳንቲም ዩሮ በላይ ኪሳራ ደርሷል ተብሏል

-የአእምሮ ችግር እንዳሌለበትም ተረጋግጧል

ፍትሕ ሚኒስቴር በረዳት አብራሪ ኃይለመድን አበራ ላይ የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ሌሊት የበረራ ቁጥር ET 702 የሆንን ቦይንግ አውሮፕላንን ከእነ 202 ተሳፋሪዎቹ ወደ ሮም በሚበርበት ወቅት ጠልፎ ሲውዘርላንድ አሳርፏል በማለት በከፍተኛው ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ክስ መመስረቱን የፍትሕ ሚኒስቴር ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል፡፡
በኃይለመድን ላይ የቀረበው ክስ ሁለት ሲሆን፤ የመጀመሪያው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 507/1/ ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፡-
‹‹…በዋና አብራሪ ፓትዮዝ ባርቤሪ አማካኝነት ከአዲስ አበባ በሱዳን በኩል ወደ ጣሊያን ሀገር ሮም ከተማ መንገደኞችን ለማድረስ በማጓጓዝ ላይ እንዳለ ዋናው አብራሪው የበረራ መቆጣጠሪያውን ክፍል ከውስጥ በመቆለፍ፣ ያለፍቃድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ አውሮፕላኑን በቁጥጥር ሥር በማድረግ የአውሮፕላኑ የበረራ ቡድን አባላት በሩን እንዲከፍት ሲጠይቁት አርፋችሁ የማትቀመጡ ከሆነ በአውሮፕላኑ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ብሎ በማስፈራራት፤ እንዲሁም የአውሮፕላኑን የመዳረሻ አቅጣጫ ያለአግባብ በማስቀየር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ፈቃድ ውጭ ወደ ስዊዘርላንድ አየር ክልል ውስጥ በመግባት ተሳፋሪዎች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ሕይወት እና ደህንነት አደጋ ላይ እንዲወድቅ አድርጎ በመጨረሻ በጄነቭ ከተማ ውስጥ ያለመዳረሻው እንዲያርፍ በማድረጉ እና ተሳፋሪዎችን ለአደጋ በማጋለጡ በፈፀመው በሕገ-ወጥ መንገድ በጉዞ ላይ ያለን አውሮፕላን መያዝ ወይም ማገት›› የተከሰሰ መሆኑን ያትታል፡፡
በሁለተኛነት የተመሰረተብት ክስ ደግሞ በዚሁ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 508/1/ ላይ ያለውን መተላለፍ የሚል ሲሆን፤ ክሱም በአጭሩ እንዲህ ይላል፡-
‹‹…ያለፍቃድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ አውሮፕላኑን በቁጥጥር ሥር በማድረግ የአውሮፕላኑ የበረራ ቡድን አባላት በሩን እንዲከፍተው ሲጠይቁት አርፋችሁ የማትቀመጡ ከሆነ በአውሮፕላኑ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ በማለት በማስፈራራት አውሮፕላኑን በድንገት እና በፍጥነት ሁለት ጊዜ ከፍ እና ዝቅ (dive) በማድረግ በአውሮፕላኑ ውስጥ ያሉትን የመንገደኞች ምግብ ማቅረቢያ ቁሳቁሶች እንዲገለባበጡ በማድረግ፣ የአውሮፕላኑን የመዳረሻ አቅጣጫ ያለአግባብ በማስቀየር፣ ከአትዮጵያ አየር መንገድ ፈቃድና እውቅና ውጭ ስዊዘርላንድ አየር ክልል ውስጥ በመግባት ስዊዘርላንድ ከተማ ጀኔቭ በመግባት አየር ላይ በማንዣበብ ከቆየ በኋላ እንዲያርፍ በማድረግ በፈፀመው በሕገ-ወጥ መንገድ በጉዞ ላይ ያለን አውሮፕላን አስጊ ሁኔታ ላይ መጣል ወንጀል ተከሷል፡፡››
በፌ/አቃቤ ሕግ ብርሃኑ ወንድምአገኝ ፊርማ ለፍርድ ቤቱ የቀረበው ማመልከቻ ከስ ቻርጁን ጨምሮ አስራ አንድ ገፅ ሲሆን፤ የዋና አብራሪው፣ የአምስት የበረራ አስተናጋጆች እና የአራት ሰዎች ስም ዝርዝር በመስክርነት ተገልፆአል፡፡ በሰነድ ማስረጃነት ደግሞ አየር መንገዱ በ27/6/06 ዓ.ም ለፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ የጻፈው አራት ገጽ እና ሲቪል አቬየሽን በ21/6/06 ኃይለመድንን በተመለከተ የጻፈው ማብራሪያ ከነአባሪው ሁለት ገጽ ቀርቧል፡፡
የኃይለመድን አበራን የጤንነት ሁኔታ በተመለከተ አየር መንገዱ ለፌደራል ፖሊስ በላከው ደብዳቤ በስድስት ወር ውስጥ አምስት ጊዜ ያህል ለቀላል ሆድ ቁርጠት፣ ራስ-ምታት፣ ጉንፋንና ተቀምጥ ወደ ድርጅቱ ክሊንኪ ከመሄዱ ያለፈ ምን ችግር ያሌለበት ጠኔኛ እንደሆነ ገልፆአል፡፡ ሲቪል አቬሽንም በተመሳሳይ መልኩ በላከው ደብዳቤ አብራሪው አመታዊ የጤና ምርምራ አድርጎ እ.ኤ.አ. እስከ 22/12/2014 ዓ.ም ድረስ ጤነኛ መሆኑን ማረጋገጫ ሰርተፍኬቱን አድሶ እንደሰጠው አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ ከዚሁ ጋር አያይዞ ሁለት መቶ ሀምሳ ሶስት ሺህ፣ ሶስት መቶ ሰላሳ ስድስት ብር ከአራባ ሁለት ሳንቲም ዩሮ ኪሳራ እንደደረሰበት እና በቀጣይም ተጨማሪ ክፍያዎች እንደሚኖሩበት ገልፆአል፡፡ እንደ ምንጮቼ አገላለፅ መንግስት ክሱን በሚስጥር የያዘው ሲሆን፤ እስካሁንም በሚቆጣጠራቸው ሚዲያዎቹ ላይ ጉዳዩን በዜና እንዲገለፅ አላደረግም፡፡
የሆነው ሆኖ ዋናው ጥያቄ ኃይለመድን ጠለፋውን ባፈፀመበት ወቅት ‹‹እብድ›› (የአእምሮ ችግር ያለበት) ለማስመሰል የተደረገው ሙከረ ውሸት እንደሆነ በአየር መንገዱና በሲቪል አቬሽን ተፅፈው ከክሱ ጋር የተያያዙት ደብዳቤዎች በማረጋገጣቸው፣ የጠለፋው ምክንትያት ምንድን ነው? የሚለው ይመስለኛ፡፡ በርግጥ ምንም እንኳ ምክንያቱን አብራሪው በሲዊዘርላንድ ፍርድ ቤት ቀርቦ እሲኪናገር መጠበቅ እንዳለብኝ ባልዘነጋም፤ በግሌ እጅግ አፋኝና ነውረኛ የሆነው ሥርዓት ላይ ያለውን ተቃውሞ ለመግለፅ ያደረገው ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ይህ እውነት ከሆነ ደግሞ ኃይለመድንን ሊወቀስና ሊወገዝ የሚችልበት ነገር የለም፡፡ አየር መንገዱ የሕዝብ መሆኑ ባይካድም፤ በአሁኑ ወቅት የጥቂት ጉምቱ ባለሥልጣናት መፈንጫ እና ኪስ ማደለቢያ መሆኑ መዘንጋት የለበትምና፡፡
ከዚህ አንፃርም ከሀገር ውጪ ላሉ ወገኖቼ ሁለት መልዕክት ማስተላለፍ እወዳለሁ፡፡ የመጀመሪያው የኃይለመድን ስልት ዞሮ ዞሮ በሰላማዊ ትግል ማዕቀፍ ውስጥ መውደቁ የማይቀር ነውና፣ ጉዳዩ በጀብደኝነት አሊያም የተሳፋሪዎችን ደህንነት አደጋ ላይ በማይጥልና ኃላፊነት በሚሰማው፣ ሙያውንም ሆነ የወሰደው እርምጃ የሚኖረውን ውጤት አስቀድሞ በሚያውቅ የተፈፀመ በመሆኑ ዓለም አቀፍ ማሕበረሰቡ ላይ ግፊት በማድረግና ጉዳዩ ጭቆናን ከመቃወም ጋር እንደሚየያዝ በማሳመን ከተጠያቂነት የሚድንበትን መንገድ ማፈላለግ ላይ ማተኮር ሲሆን፤ ሁለተኛው ኢህአዴግ እስርኞችን በማሰቃየት ግንባር ቀደም በመሆኑ ተላልፎ እንዳይሰጠው ከጎኑ መቆም ማድረግ ላይ እንድታተኩሩ (ምናልባት ከክሱ ጋር የተያያዙ ማስረጃዎች የምትፈልጉ የሕግ ባለሙያዎች እዚህ ጋ በአታችመንት ከተቀመጡት ዶክመንቶች በተጨማሪ በኢሜል ልልክላችው እችላለሁ)
በመጨረሻም የግፍ አባት የሆነውን ነውረኛ ሥርዓት ለመቀየር (አማራጮቹ እየጠበቡ በመሄዳቸው) እንዲህ አይነት መንገዶችንም ግምት ውስጥ ማስገባት የግድ እንደሆነ መረደት ይኖርብናል፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
Link:-http://ecadforum.com/Amharic/archives/11761/

Saturday, April 12, 2014

በኖርዌ የሚገኙ የወያኔ ሰላዮችን በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በኦስሎ ከተማ ተካሄደ


ማርች 11, 2014 በኖርዌ የሚገኘው የኢትዮጵያን የስደተኞች ማህበር ያዘጋጀው ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ከተለያዩ የኖርዌ ከተሞች በመጡ ታዳሚዎች እና በኦስሎ ነዋሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያ ባንዲራ እንዲሁም በተለያዮ መፈክፎች ታጅቦ በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ። 

የዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ዋና አላማ በኖርዌ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀው በሚኖሩበት ሐገር እንደሚሰለሉ እና የወያኔ ሰላዮች በኖርዌይ ምድር መኖራቸውን የኖርዌ የደህንነት ፓሊስ ለሀገሪቱ ትልቅ ጋዜጣ መረጃ መስጠታቸውን እና በተመሳሳይ የሂውማን ራይትስ ዋች በቅርቡ ያወጣውን መረጃ መሰረት በማድረግ የኖርዌ መንግስት ለወያኔ ሰላዬዮች የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያቆም እና አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ ለመጠየቅ እና ኖርዌ በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ ያላትን የአሳይለም ፖሊሲ እንድታስተካክል የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ ነበር።

ፕሮግራሙ ከቀኑ 12፡00 የተጀመረ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ምክትል ሊቀመንበር ሰፋ ያለ የወያኔ ሰላዮችን የተመለከተ ንግግር ያሰሙ ሲሆን የዚሁ ድርጅት የሴቶች ክፍል ተወካይ ወ/ሪት ሔለን ንጉሴ አጠቃላይ በኖርዌ ያሉ ሰላዮችን እና በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ በመስጠት ሴቶች በሁለገብ ትግል ውስጥ ያላቸውን ጉልህ ሚና እንዲሁም ወደፊት ሊኖራቸው የሚገባውን ሚና ጨምረው በማስረዳት ለትግሉ አጋር መሆናቸውን ገልፀዋል። በመቀጠል የስደተኛ ማህበሩ ፀሐፊ ወ/ሪት የሺሃረግ በቀለ ሰፋ ያለ ማብራሪያ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ያቀረበች በመሆኑ የሐገሪቱ ዜጎች መልክቱን በደንብ እንዲሰሙ ያደረገች ሲሆን የኖርዌጅያን ተወላጅ የሆኑትና በስደረኞች ጉዳይ ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች ተወካዮች በተመሳሳይ ስለ ኢትዮጵያ አምባ ገነን መንግስት ከስደተኛው በላይ የሚያውቁትን መረጃ በዝርዝር በየተራ በንግግር አሰምተዋል። ይህንን የሰላማዊ ሰልፍ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ የመሩልን የስደተኛ ማህበሩ የኮሚቴ አባላት የሆኑት አቶ ዮናስ እና አቶ ጌታቸው ናቸው።

በመጨረሻም ከሰላማዊ ሰልፉ በኋላ በወ/ሮ ሰዋሰው እና በባለቤታቸው የተዘጋጀ የምሳ ግብዣ የተከናወነ ሲሆን የስደተኛ ማህበሩም የውይይት ጊዜ አዘጋጅቶ የነበረ በመሆኑ የስደተኛ ማህበሩን የሶስት ወር ሪፖርት ካቀረበ በኋላ በቀጥታ ወደ ውይይት በመግባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በኖርዌ ስለሚገኙ የወያኔ ሰላዮች በሰፊው ምክክር አድርገው ወደፊት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እንዴት እነኚህን ሰላዮች በምን መልኩ ማጋለጥ እንዳለባቸው ተወያይተው በመቀጠል አጠቃላይ ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ውይይት አድርገው ፕሮግራሙ በተሳካ ሁኔታ ከምሽቱ 19፡00 ተጠናቋል። watch the video
Link:-http://helennigussie.blogspot.no/2014/04/blog-post_11.html?m=1

Thursday, April 10, 2014

ከአገር መውጣት የማይችሉ ባለሥልጣናት በጭንቀት ውስጥ ናቸው

"አሁን ያለው ኢህአዴግ ላዩ በቀለም ቀቢ የተዋበ ይመስላል"
ኢህአዴግ በሙስና ስም የ”ማጥራት ዘመቻ” ማካሄዱን ተከትሎ የተከሰተው አለመተማመንና እርስ በርስ በጥርጥር የመተያየት ችግር ካድሬውን ማስጨነቁ ተጠቆመ። ኢህአዴግን ለመሰናበት የሚፈልጉ በርካታ ካድሬዎች “ለምን” በሚል የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመፍራት የግድ ፓርቲውን መስለው እንደሚኖሩ ተገለጸ።
የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ቀደም ሲል ኢህአዴግን ተሰናብተው የወጡና በተለያዩ የውጪ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው በማገልገል ላይ ካሉ ያገኘውን መረጃ በመጥቀስ እንደዘገበው፣ የቀድሞ የትግል ጓደኞቻቸው “በደህና ጊዜ ተገላገልክ” በሚል በፓርቲው ውስጥ ችግር ስለመኖሩ እየነገሯቸው ነው። አብዛኞቹ ኢህአዴግን ተለይተው በሰላም ስለመኖር እንደሚያስቡ ነው የተሰማው።
የቤተሰቦቻቸው የወደፊት እድልና የነሱ በፍርሃትና በጭንቀት መኖር አሳዛኝ እንደሆነ የነገሩት የቀድሞ የኢህአዴግ ሰዎች “አሁን ያለው ኢህአዴግ በቀለም ቀቢ የተዋበ ይመስላል” በማለት አንድ በሚኒስትር ዲኤታ ማዕረግ እያገለገለ ያለ የቀድሞ ጓደኛቸው እንደነገራቸው ገልጸዋል።
ለስራ እንኳን ካገር መውጣት የማይችሉ ባለስልጣኖች እንዳሉ ዘጋቢያችን አመልክቷል። በተቀመጡበት ሃላፊነት ወደ ውጪ የሚያስኬድ አጋጣሚ ሲኖር የሚከለከሉ እንዳሉም ያገኛቸውን መረጃዎች ጠቅሶ ዘግቧል። ለሃላፊዎቹ ደህንነት ሲባል የሚሰሩበትን ተቋምና ስም መናገር እንደማይችሉ በመጥቀስ መረጃውን የሰጡት ክፍሎች “ባለስልጣኖቹ በመካከላቸው እርስ በርስ መተማማን ስለማይችሉ ችግራቸውን መወያየት እንኳን አይችሉም” ብለዋል፡፡
“በጣም የሚቀርቡኝ ጓደኞቼ ገንዘብ ወደ ውጪ እንድወስድላቸው እስከመጠየቅ ደርሰዋል” ሲሉ የገለጹት የቀድሞ የኢህአዴግ ባለስልጣን፣ ፓርቲው በሙስና ስም ያካሄደው የሽግግር ወቅት የማጥራት ርምጃ የፈጠረው ስሜት አሁን ድረስ እንዳለ ጠቁመዋል።
ሰሞኑንን ወደ አሜሪካ ያቀኑ የቀድሞ የኢህአዴግ ሰው በማግኘት ተመሳሳይ መረጃ ያሰባሰበው ዘጋቢያችን “ኢህአዴግ በከፍተኛ የመበስበስ አደጋ ውስጥ ይገኛል። በዚህም የተነሳ ካድሬው ተዥጎርጉሯል” ሲል ሪፖርት አድርጓል። ኢህአዴግ በውስጥ ያለበትን ችግር ለማድበስበስ የአባይ ግድብ ላይ ትኩረት በመስጠት “የንቅናቄ ሃይል” በማስፋፋት ላይ እንደሆነም ጠቁሟል።
ድፍን ህዝብ የአባይ ግድብን አስመልክቶ ያለው ስሜት በበጎ መልኩ የሚታይ በመሆኑ ኢህአዴግ ይህንኑ የህዝብ ስሜት ለቅስቀሳና ለበሽታው መደበቂያ ለማድረግ እየተጠቀመበት እንደሆነ ተጠቁሟል። የህጻናት ፕሮግራሞች ሳይቀሩ አባይ ላይ ያነጣጠሩ ቅስቀሳዎች እያስተላለፉ መሆናቸውን ያመለከቱት ሰው፣ “ስለ አባይ ግድብ የሚባለውና የሚሰራው ፕሮግራም ችግር የለውም። በአግባቡ ቢሰራበት ብሔራዊ ስሜት ሊገነባበትም በተቻለ ነበር። ይሁን እንጂ ዓለማው የችግር ማለባበሻ እንዲሆን መደረጉ ነው” ብለዋል።
“መለስ ኢትዮጵያን ቢወድ ኖሮ ከባድመ ጦርነት በኋላ የፈረሰውን ብሔራዊ አንድነትና መግባባት መልሶ መትከል ይቻል ነበር” በማለት የተናገሩት እኚሁ ሰው “በወቅቱ ይህንን ሃሳብ ያነሱ ሰዎች ነበሩ” ሲሉ ቁጭታቸውን ይሰነዝራሉ። በማያያዝም ኢህአዴግ የአባይን ግድብ ተንተርሶ ብሔራዊ አንድነት የሚገነባበት፣ መቀራረብና በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር ብሔራዊ መግባባት የሚደረስበት፣ ለወደፊቷ ኢትዮጵያ መሰረት የሚጣልበት ቢያደርገው እውነተኛው የኢትዮጵያ ህዳሴ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል።
በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝን በውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም ለመተካት ህዋሀቶች የሚያደርጉት ሽርጉድ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ሪፖርት መቅረቡ ተሰምቷል። ይኽው ሪፖርት የቀረበላቸው ክፍሎች ቀደም ሲል እንዳደረጉት የህወሃትን ከፍተኛ አመራሮች በማነጋገር ስህተት እንዳይሰሩ እየወተወቱ ነው።
Link;-http://www.goolgule.com/officials-who-are-forbidden-from-leaving-the-country-are-in-despair/