Tuesday, September 30, 2014

አስደንጋጭና አሳፋሪ ምስጢር ሲገለጥ፡ Shocking!

አስደንጋጭና አሳፋሪ ምስጢር ሲገለጥ፡ Shocking!

Sept 21, 2014
በሴቭ አድና
ትላንት ሀይማኖተኛ፣ ፈሪሀ እግዚአብሄር የያዘና ጨዋ የነበረ ህዝብ እንዴት እንዲህ በሙስና፣ የንዋይ ፍቅርና በውሸት እንዲህ ረከሰ?
ባንድ ነገር መስማማት እንችላለን፡፡ የዛሬ አያድርገውና ህዝባችን ሙስናን፣ ስርቆትን፣ ውሸትን፣ ጭቆናን የሚፀየፍ፤ ተካፍሎ መብላትን እንጂ መስገብገብን የማይሆንለት፤ ክብሩን የጠበቀ፣ የሌላ መብትም የማይነካ ኩሩና በራስ መተማመን የተጎናፀና ከፍ ያለ የሞራል እሴቶች የነበሩት ነበር፣ ከአንድ ሁለት ዐስርት ዐመታት በፊት፡፡
አንዳንዶች ጥቂት አባባሎችን (ለምሳሌ “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” የሚለውን የአማርኛ ምሳሌ) እያነሱ “ባህላችን ሙስና ያበረታታል” ለማለት ዳርዳር ቢሉም ማለት ይህ ከእውነታ የራቀ ነው፡፡

Monday, September 8, 2014

የዓመቱ አነጋጋሪና አወዛጋቢ ክስተቶች

  • 1584
    Share
በዓመቱ መጀመሪያ በመስከረም ወር 2006 ዓ.ም ለ12 ዓመታት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፤ ከስልጣናቸው የወረዱ ሲሆን በቦታቸውም ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ተተክተዋል፡፡ በአምባሳደርነት ዘመናቸው የውጭ አገር ኢንቨስተሮችን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣትና አገር ውስጥ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በማግባባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው የሚነገርላቸው ዶ/ር ሙላቱ፤ የፕሬዚዳንትነት ስልጣናቸውን ከተረከቡ በኋላም ሥራቸው በቤተመንግስት አካባቢ የተገደበ አልሆነም፡፡ በተለያዩ አገራት እየዞሩ የውጭ ኢንቨስተሮችን የማግባባት ሥራቸውን ቀጥለውበታል፡፡
fe32ef4893ac92d41e13984d3a7fb0e2_XL
በዓመቱ ከተከናወኑ አነጋጋሪ ጉዳዮች መካከል አንድነት ፓርቲ ከሰላማዊ ሰልፍ ጋር በተገናኘ የመብት ጥሰትና መጉላላት ተፈጽሞብኛል በማለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባንና የከተማዋን ፖሊስ ኮሚሽን በፍ/ቤት መክሰሱ ተጠቃሽ ነው፡፡
ፍ/ቤቱም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ “ክሱ ለክስ የሚያበቃ ምክንያት የለውም፣ አስተዳደራዊ ውሣኔ ያገኝ የሚል ውሣኔ የሰጠ ሲሆን ፓርቲውም በጊዜው ይግባኝ እንደሚጠይቅ ገልፆ ይግባኝ ለመጠየቅ በሂደት ላይ ይገኛል፡፡
የቀድሞ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ እንዲሁም የኢዴፓ መስራችና ሊ/መንበር የነበሩት አቶ ሙሼ ሰሙ ራሳቸውን ከፖለቲካ ፓርቲ ያገለሉት በዚሁ ባሳለፍነው ዓመት ነው፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ከጤና ጋር በተያያዘ፣ አቶ ሙሼ ደግሞ “የጥሞና ጊዜ እፈልጋለሁ” በሚል የፓርቲ ፖለቲካ በቃን ብለዋል፡