Thursday, July 30, 2015

ኦባማ በአዲስ አበባ

July 29, 2015
ይገረም አለሙ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ በአዲስ አበባ ጉብኝታቸው ከጠቅላይ ምኒስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝ ጋር በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት በሰላማዊ ምርጫ የተመረጠ ብለዋል በሚል ከተለያየ አቅጣጫ ተቃውሞና ነቀፌታ እየተሰነዘረባቸው ነው፡፡ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ባደረጉት ንግግር ምርጫው በሰላማዊ ሁኔታ ተካሂዷል ይህ ማለት ግን ዴሞክራሲያዊ ነው ማለት አንዳልሆነ ከአቶ ኃይለማሪያም ጋር መነጋገራቸውን ስም ጠቅሰው ተናግረዋል፡ ምርጫ ግዜ እየጠበቁ ማድረግ ብቻ ሳይሆን ነጻና ፍትሀዊ መሆን አንዳለበትም አስረግጠው ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረቱ ንግግራቸው እስካሁን ተቃውሞ አልተሰማበትም፡፡
Obama in Addis Ababa, Ethiopia
የዚህች ጽሁፍ አላማ ኦባማ ስለተናገሩት ማውሳት አይደለም፤በተለይ ሀገር ቤት ያሉ ተቀዋሚዎች ሰላማዊ ምርጫ የሚለውን አገላለጽ ሲቃወሙ አንድም ትናንትን የረሱ ሁለትም በሚቃወሙት ድርጊት ውስጥ የእነርሱ ድርሻ መኖሩን ያልተገነዘቡ ሆኖ ስለተሰማኝ ይህን ለማመለከት ነው፡፡ ትናንትን መርሳትና ራስን ነጻ አድርጎ ሌላውን መውቀስና መኮነን ስር የሰደደ ችግራችን ነው፡፡ ከዚህ መላቀቅ ካልቻልን ደግሞ ለውጥ ናፋቂ ሆነን መኖራችን አይቀሬ ነው፡፡
ወያኔ የምርጫ 97 ሽንፈቱን የቀለበሰው በጠመንጃው ብቻ ነው ብለን እናምን ይሆናል፤ነገር ግን አይደለም፤ ቅድመ ምርጫም ሆነ ድህረ ምርጫ የአሜሪካ ረዥም እጅ ነበረበት፡፡ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ቅንጅት ስልጣን ቢይዝ በወያኔ የምታገኘው ጥቅም መቀጠሉ ለአሜሪካ አጠራጣሪ ነበርና ነው፡፡አሜሪካ በግልጽ የማይታወቁ ብዙ ነገሮች ኢትዮጵያ ውስጥ አሏት፡፡ የአርባ ምንጩን የሰው አልባ አውሮፕላን ጣቢያ አንድ አሳ ጎርጓሪ ጋዜጠኛ እስከሚያጋልጠው ድረስ ማን ያውቅ ነበር?

Friday, July 10, 2015

ዘላለም ወርቃገኘሁ ማን ነው? ( በላይ ማናዬ )

July 10, 2015
ከዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ወዳጅ ጋዜጠኞች የእስር ዜና ትንሽ ዘግይቶ ልክ የዛሬ አመት ሐምሌ 1/2006 ዓ.ም ነበር በአደባባይ ስማቸው ጎልቶ የወጡት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳንኤል ሺበሽና ‹‹የሰሜኑ ፈርጥ›› አብርሃ ደስታ መታሰራቸው በሰዓታት ልዩነት ይፋ የሆነው፡፡ እነዚህ ሰዎች በታሰሩበት ወቅት ግን ሌላ ማን አብሯቸው እንደታሰረ ማናችንም ቢሆን ለሚዲያ በበቃ ዜና የሰማነው ነገር አልነበረም፡፡ በቀናት ጊዜያት ውስጥ የፓርቲ አመራሮቹ በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ስለመታሰራቸው በሰማንበት ጊዜ እንኳ አብረው የታሰሩ ሰዎች ስለመኖራቸው አላወቅንም ነበር፡፡ጋዜጠኛ ዘላለም ወርቃገኘሁ
ተጠርጣሪዎቹ በእስር ከነበሩበት ማዕከላዊ ምርመራ ወደ አራዳ ፍርድ ቤት በቀረቡ ጊዜ በቦታው ተገኝቶ የታሰሩትን የፓርቲ አመራሮች ለማየትና አጋርነት ለማሳየት ብዙ ሰው ይገኝ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ግን አንድ ቀጭን ወጣት ከፓርቲ አመራሮች ቀድሞ በፌደራል ፖሊሶች ታጅቦ ወደ ፍርድ ቤት ይመጣ ነበር፡፡ የልጁን ማንነትና የተያዘበትን ምክንያት ለማወቅ ቤተሰቦቹ ናቸው ብዬ ያሰብኳቸውንና በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ያገኘኋቸውን ሰዎች መጠየቄ አልቀረም፡፡ ዳሩ ግን ቤተሰቦቹም ሆነ ጓደኞቹ ስለዚህ ቀጭን ወጣት መናገር አልፈለጉም፡፡ ፎቶውን ቢሰጡኝና መረጃ ማግኘት ብችል ለሚዲያ ላበቃው እንደምፈልግ ብገልጽላቸውም ልንግባባ አልቻልንም፡፡ ለካ ቤተሰቦቹ ዝምታን የመረጡት የወጣቱ አቋም ‹‹ወደ አደባባይ›› መውጣትን ካለመፈለጉ የመነጨ ኖሯል፡፡
ወጣቱና የፓርቲ አመራሮቹ አራት ወራት የምርመራ ጊዜያቸውን አጠናቅቀው ከማዕከላዊ ሲወጡና በይፋ ክስ ሲመሰረትባቸው የዚህ ቀጭን ወጣት ስም ከሁሉም ቀድሞ ተገኘ፤ አዎ በዚህ ወጣት ስም በተከፈተ መዝገብ አስር ሰዎች የሽብር ክስ ተመሰረተባቸው…በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ፡፡ አሁን ቤተሰቦቹም ሆነ ወጣቱ ራሱን መደበቅ አላስፈለገውም-አይችልምም፡፡ እናም ሚዲያዎች የፓርቲ አመራሮችን ጉዳይ ሲከታተሉ ‹‹በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ…›› እያሉ ስሙን ወዳልፈለገው አደባባይ አወጡት፡፡
ዘላለም ወርቃገኘሁ ማን ነው?
በአፍሪካ ውስጥ የፖለቲካ ህይወትን በእስር መጀመር፣ መጨረስ፣ አሊያም ደግሞ እንደ አቅም ግንባታ ስልጣና መሐል ላይ በሰቆቃ የተሞሉትን እና ኢ-ሰብዓዊ የሆነ የምርመራ መንገድ የሚከተሉትን የአምባገነኖች ደህንነት ሰራተኞችን በትር ቀምሶ መውጣት የተለመደ ነው፡፡ ዘላለም ወርቃገኘሁ ግን በፍጹም በዚህ መልኩ በፖለቲከኝነት አደባባይ እወጣለሁ ብሎ አላሰበም ነበር፡፡ ለመሆኑ ‹‹ዘላለም ወርቃገኘሁ ማን ነው? እንዴት እንደ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሽ፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ ያሉ እውቅ የፖለቲካ ስብዕናዎች (personalities) ባሉበት መዝገብ ሊከሰት ቻለ?››
የተወለደው አዲስ አበባ፣ አዲሱ ገበያ አካባቢ ነው፡፡ ሰፊ ቤተሰብ ውስጥ (11 ልጆች ያሉበት ቤት) የመጨረሻ ልጅ ነው፡፡ አባቱ አርቲስት (አሁን በህይወት የለም) ነበር፤ እናቱ ደግሞ ጡረታ የወጣች የመንግስት ሰራተኛ ናቸው፡፡ ዘላለም መካከለኛ ገቢ ያለውና ከፍተኛ የልጆች ነጻነት ባለበት አስተዳደግ ማለፉን ይናገራል፡፡ እንዲያውም አባቱ የአገዛዙ የ‹ዴሞክራሲ› ዲስኩር ሲያሰለቸው ‹‹እኔ ቤት ዴሞክራሲ ከቃሉ በፊት ተግባሩ ነው የገባው›› ይል እንደነበር ያስታውሳል፡፡ ዘላለም ትምህርቱን የተከታተለባቸው ት/ቤቶች መጠሪያ በራሱ አሁን ላለው የኢትዮጵያዊነት ስሜት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሳያደርጉ አልቀሩም፡፡ አንደኛ ደረጃን ‹‹ኢትዮጵያ ዕድገት››፣ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃን (7ኛ እና 8ኛ ክፍል) ‹‹አርበኞች››፣ እና ሁለተኛ ደረጃን ‹‹ኢትዮጵያ ትቅደም›› ት/ቤቶች ተከታትሏል፡፡ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን አጠናቅቋል፡፡ የዛሬ አንድ አመት በስርዓቱ የደህንነት ኃይሎች በተያዘበት ጊዜም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ አስተዳደር ት/ት ክፍል በፐብሊክ ፖሊሲ አናሊስስ (Public Policy Analysis) የማስተርስ ዲግሪውን ለመጨረስ የቀረው የመመረቂያ ጽሑፍ ማዘጋጀት ብቻ ነበር፡፡
የዘላለም የእምቢተኝነት መሰረት
ቤተሰብ ነጻ አስተሳሰብን የሚያራምድ እና መብቴን አላስረግጥም የሚል ትውልድ ለመፍጠር መሰረት ነው፡፡ በእርግጥ የአካባቢና የቤተሰብ አስተዋጽኦም ከቤተሰብ የተናነሰ አይደለም፡፡ ዘላለም የፖለቲካ አስተሳሰቡ በአስተዳደጉ የተቀረጸ እንደሆነ ያምናል፡፡ የሦስተኛ ክፍል ተማሪ እያለ አሁን ላይ በማያስታውሰው ምክንያት የእንግሊዝኛ መምህራቸው በመደዳ የክፍሉን ተማሪዎች መቅጣት ትጀምራለች፡፡ የመጀመሪያዎቹን ሦስት ተማሪዎች እንደገረፈች ዘላለም ከመቀመጫው ተነስቶ በተከፈተው በር ሩጦ በመውጣት ወደ ርዕሰ መምህሩ ቢሮ ያመራል፡፡ ራሱን ከድብደባው ካተረፈ በኋላ የሆነውን ሁሉ ለርዕሰ መምህሩ አስረዳው፡፡ ርዕሰ መምህሩ ይዞት ወደ መማሪያ ክፍሉ ሲመለሱ የጅምላ ቅጣቱ እየተካሄደ ደረሱ፡፡ ብዙዎች ተማሪዎች ያለቅሳሉ፡፡ አንዳንዶቹ በተለየ ሁኔታ እጃቸው ሰንበር በሰንበር ሆኗል፡፡ ርዕሰ መምህሩ በጣም ተናዶ እንግሊዝኛ መምህራቸው ላይ ጮኸባት፡፡ በዚህም እሷን ከክፍል አስወጥቶ ተማሪዎቹን አረጋጋ፡፡ ዘላለምም በእቢተኝነት ውጤት አሳየ፡፡ ‹‹ያኔ የሚደግፈኝ ስላገኘሁ የልጅነት ልቤ ኩራት ተሰማት፡፡ አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው ያቺ የመጀመሪያዋ እምቢተኝነቴ በርዕሰ መምህሩ ድጋፍ ባታገኝ ኖሮ አሁን ያለኝን ጭቆናን የማይቀበል ባህሪ አላገኘውም ነበር›› ይላል ዘላለም፡፡
ይህ ሦስተኛ ክፍል ላይ መብትን ባለማስረገጥ የተጀመረው እምቢተኝነቱ ከፍ ወዳለ ደረጃ የተሸጋገረው በ1991 (የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት) የተማሪዎች ም/ቤት ፀሐፊ በነበረበት ጊዜ ነበር፡፡ በወቅቱ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞችን ያቀፈ ኮሚቴ ተቋቁሞ ነበር፡፡ የኮሚቴው ዓላማ ለጦርነቱ ገቢ ማሰባሰብና የደም ልገሳን ማስተባበር ነበር፡፡ ዘላለም ኮሚቴው ውስጥ የገባው ተማሪውን በመወከል ቢሆንም ያለኮሚቴው እውቅና የት/ቤቱ አስተዳደር ማህተም ያረፈበት ደብዳቤ ቦርድ ላይ በመለጠፍ ‹‹የወታደሮች ምልመላ›› ያደርግ ጀመር፡፡ ዘላለም ይህንን በመቃወም በመጀመሪያ የተማሪዎች ም/ቤት አስፈጻሚዎችን በተቃውሞ አሳመጸ፡፡ በመቀጠልም የትምህርት ቤቱ አስተዳደር የኮሚቴውን ሰብሰባ እንዲመራ፣ አለበለዚያ በተማሪዎች ም/ቤት ማህተም ምልመላውን የሚቃወም ማስታወቂያ የመጻፍ ግዴታ እንዳለበት አሳሰበ፡፡

ስለ እውነት፣ ስለፍትሕ እናት ኢትዮጵያ አሁንም ትጮኻለች!!

July 9, 2015
በዲ/ን ተረፈ ወርቁ
Few bloggers and journalists freed in Ethiopia
የኢሕአዴግ መንግሥት አሸባሪዎች ናቸው፣ በዜጎች ክቡር ደም የቆመውን ሕገ መንግሥቱን በኃይል ለመናድ የተደራጁ ናቸው፣ በውጭ አገር ካሉ ሰላማችን፣ ዕድገታችን በቅናት ብግን እያደረጋቸው ካሉና አገራችንን ለማተራመስ ቆርጠው ከተነሡ ከፈረደበት ሻቢያ፣ ሽብርተኛ ድርጅቶችና ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር አብረው ይሠራሉ፣ የአገርንና የሕዝብን ደኅንነትና ፀጥታ አደጋ ላይ ጥለዋል፣ በኢትዮጵያ ሰላምና በሕዝቦቿ ልዑላዊነትም ላይ በመደራደር ይቅር የማይባል ክህደት ፈጽመዋል ያላቸውን የዞን ፱ ጦማርያንና ሌሎች ጋዜጠኞችን ከአንድ ዓመት በላይ ፍርድ ቤት ሲያመላልሳቸው ቆይቷል፡፡
ማብቂያ የሌለው በሚመስል ቀጠሮ በነጋ ጠባ ወደ ፍርድ ቤት ሲመላለሱ የቆዩ ወገኖቻችንም ያን አምኖ ለመቀበል ቀርቶ ለመስማት እንኳን የሚከብድ ክስና የወንጀል ማስረጃ አቅርቤባችኋለኹ ያላቸውንና ፍርዳቸውን ከእውነት፣ ከፍትሕ አምላክ ሲጠብቁ የነበሩ ወገኖቻችንን መንግሥት በነጻ ተሰናብታችኋል ሲል የመለቀቃቸውን ዜና እንደ ዋዛ አበሰረን፡፡ መንግሥት እነዚህን ወገኖቻችንን በነጻ ያሰናበተበትን ምክንያቱን አልነገረንም፡፡ ቅሉ እንዲነግረንም የምንጠብቀው ሰዎችም ያለን አይመስለኝም፡፡
ኢሕአዴግ እንደቀደመው ጊዜም መንግሥት መሐሪ ነውና በአገርና በሕዝብ ላይ ላደረሳችሁት ክህደትና ወንጀል ይቅርታ ጠይቁና ነጻ ውጡ የሚለውን የተለመደች ብልጣብልጥነቱንም አልተጠቀመም፡፡ በዚህ ሰበብም ሽማግሌዎችንም እነዚህን ሰዎች እባካችሁ ማልዱኝ፣ አማልዱኝ በሚል አላደከመም፡፡ እንደው ብቻ ደርሶ ነጻ እኮ ናችሁ ሲል በአንድ ሺ አንድ መረጃና ሰነድ ወንጀላቸውን፣ ኃጢአታቸውን ሰማይ የሰቀለውን እነዚህን ሰዎች በአንዲት ማዘዣ ቃል ብቻ ነጻ ናችሁ ሲል አሰናበታቸው፡፡
መቼም ዘንድሮ ኢሕአዴግ እፍረትና ይሉኝታ ይሉትን ባህላችንን አሸቀንጥሮ የጣለ ነው የሚመስለው፡፡ ምርጫውን መቶ በመቶ አሸንፌያለኹ ብሎ ባወጀ መሬት አንቀጥቅጥ ድሉ ማግሥት ደግሞ እነዚህን በአገር ልዑላዊነት በሕዝብ ጥቅም ላይ የተደራደሩ ሰዎችን ማን ወንድ ነው ፍርዳቸውን ሳያገኙ፣ የእጃቸውን ሳይከፈሉ ከእጄ የሚያወጣቸው ሲል እንዳልነበር፣ እንዳልተገዘተ ኹላ ‹‹ሾላ በድፍኑ›› እንዲሉ አበው ከአንድ ዓመት በላይ በቁጥጥር ሥር ያዋላቸውን እነዚህን ወገኖች በነጻ አሰናብቼቸዋለኹ እንግዲህ ደስ ይበላችሁ ሲል ዜናውን፣ የምስራቹን አበሰረን፡፡
እኛም መንግሥትን እንደው እነዚህን ወገኖች ስታስርም ሆነ ስትፈታ ምክንያትህ ምንድን ነበር በሚል ጥያቄ ራሳችንን ስናሞኝ አንገኝም፡፡ መንግሥት ምክንያቱ ምንም ይሁን ምንም እነዚህ ወገኖቻችን በነጻ በመለቀቃቸው የሁላችንም ደስታ፣ ሐሤትና እረፍት ነው፡፡ ሌሎችም ያለ ፍርድ የታሰሩ፣ ፍትሕን የተነፈጉ ወገኖቻችንም ነጻ ይወጡ ዘንድም ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ከዚህ ግማሽ ደስታ ባሻገር ግን አሁንም ሌላ ጥያቄ፣ ሌላ ብሶት፣ ሌላ ቁጭት አሁንም በብዙዎች ልብ ውስጥ ተከድኖ አለ፡፡
‹‹በፍርድ ከኼደች በቅሎዬ፣ ያለ ፍርድ የኼደች ቆሎዬ›› እንዲሉ አበው እንዲህ በእናት ኢትዮጵያ ምድር ስለተረገጠው እውነት፣ ስለዘመመው ፍትሕ፣ ስለተዛነፈው ፍርድ የብዙዎች ቁጭት፣ ብሶትና ምሬት ከትናንትና ይልቅ ዛሬ ተባብሶ ይቀጥላል፡፡ እናም መንግሥት ሆይ ‹‹የፍትሕ ያለ፣ የእውነት ያለኽ፣ የፍርድ ያለኽ!›› የሚለው የሕዝብ፣ የኢትዮጵያ እናቶች እንባና ጩኸት ሰማይን እንዳናወጠ፣ ምድሪቱን እንዳጨቀየ ወደ ሰማይ መፍሰሱን ቀጥሏል፡፡ ግና መንግሥት አሁንም ድረስ በዚሁ ኹሉ በሕዝብ ብሶት፣ እዬዬና እሮሮ ውስጥ የሚሰማ ጆሮን፣ የሚያይ ዓይንን የታደለ አይመስልም፡፡
ግና የራሄሎች እንባ ወደ ጸባኦት አምላክ ጆሮ በደረሰ ጊዜ፣ ያ የፍርድ ጽዋ የሞላ ጊዜ ግን… ወየው ፍርድን ለሚያጣምሙ፣ ፍትሕን ለሚያዛቡ የእውነት ጠላቶች!! እነዚህ ልባቸውን እንደ ግብጻዊው ፈርኦን ልብ ፈጽመው ያደነደኑ፣ በኢትዮጵያ አምላክ ላይ ልባቸውን ያኮሩ፣ በሕዝባቸው ላይ የጭቆናን ቀንበር ያጠበቁ፣ ፍርድንና ፍትሕን ያዛቡ፣ መበለቲቱንና ባልቴቶችን ያስለቀሱ፣ የሽማግሌዎችንም ፊት ያላፈሩ ዓመፀኞች፣ የአምላክን ወሰን የሌለውን ትዕግሥቱንና ምሕረቱን እንደ ከንቱ ነገር የቆጠሩና ያጣጣሉ አምባገነኖች ኹሉ ራሳቸውን ለመቅሠፍት፣ ለውርደት ሞት የጠበቁ፣ አጥፊው የሞት መልአክ በቤታቸው ደጃፍ አድብቶ፣ ቆሞ ያለ መሆኑን ያውቁት ዘንድ በእርግጥም የግድ ይላቸዋል፡፡

Thursday, July 9, 2015

የ ‹‹ይቅር ባይ›› መንግስት ‹‹ይቅር የማይባል›› ድርጊት!!

July 9, 2015
አሌክስ አብርሃም
‹‹በመንግስት›› ካባ የተጀቦኑት ግለሰቦች ፈፅሞ ‹‹ይቅር ባይ ›› አይደሉም!! …ይቅር የማይባል ስህተት የህዝብ ልጆች ላይ የሚሰሩ ጭፍን ጥላቻ እና የበታችነት ስሜት የተጠናወታቸው አንባገነኖች እንጅ …አሁንም ‹‹ መንግስት ›› በጭፍን ጥላቻ ያሰራቸውን በርካታ ኢትዮጲያዊያን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ … የማንንም አገር መሪ መምጣት ሳይጠብቅ ሊፈታ ይገባል ! እኛ ኢትዮጲያዊያን አባቶቻችን በከፈሉልን ንፁህ መስዋእትነት ከነድህነታችን ተከባብረንና ተፋቅረን የምንኖር የተከበርን ህዝቦች እንጅ …መንግስት ለብድርና እርዳታ ጥማቱ አበዳሪ በመጣ ቁጥር እንደዘንባባ እየዘነጠፈ ሃያላን መሪዎች እግር ስር የሚያነጥፈን ርካሽ ህዝቦች አይደለንም !!Ethiopian arrested zone 9 bloggers
እዝኛለሁ … ከእስሩ የበለጠ የተፈቱበት መንገድ አሳዝኖኛል …መንግስት ለዜጎች ያለውን እጅግ የወረደ ንቀትና ‹‹ማን አለብኝነት›› የሚያሳይ ድርጊት ነው … ኢትዮጲያዊያን ባልቴቶች በምርኩዝ ፍርድ ቤት ድረስ ሂደው እያለቀሱ ሲለምኑት በወታደር እያስገፈተረ ያስባረረ መንግስት …ህዝቦች በአደባባይ ወንድማ እህቶቻችንን ፍታልን እያልን ስንለምን ከነደጋፊወቹ ያሻውን ፀያፍ ስም እየለጠፈ ሲሳለቅና ሲያሽጓጥጥ የኖረ መንግስት… አሁን የባርነት ስነልቦናው በፈጠረው መሽቆጥቆጥ ‹‹ወደቤታችሁ ሂዱ›› ብሎ ከየቤታቸው አፍኖ የወሰዳቸውን ዜጎች መፍታቱ … ብሔራዊ ውርደት ነው !! እንዲህ አይነት ‹‹ስፈልግ አስራችኋለሁ ስፈልግ እፈታችኋለሁ ›› መልእክት ያዘለ ‹ነፃነት› ከጠባብ እስር ቤት ወደሰፊ እስር ቤት ሰዎችን ማዘዋወር እንጅ ፍትህ ያመጣው ነፃነት አይሆንም …አይደለምም!
ህገ መንግስቱን ባሻው ሰአት የሚጥስ ምንም ዋስትና ሊሰጥ የማይችል መንግስት እንዳለን ማሳያም ነው ! መንግስት እስካሁንም ባሰራቸው ጋዜጠኞች ጦማሪያንና ሌሎችም ንፁሃን ላይ ከመረረ የግል ጥላቻ ውጭ ምንም ምክንያት እንደሌለው የሚያሳይ ተቀባይነት የሌለው ድርጊት !! ህዝብን የማያከብር በህዝብ ስም እርዳታና ብድር ለመለመን የሚሽቆጠቆጥ መንግስት ለአገርም ለዜጎችም ዋስትና አይሆንም !!
ለማንኛውም አንድ አመት ሙሉ ልጆቻችሁ በግፍ ‹‹ለታገቱባችሁ›› ወላጆች… በአሜሪካ መሪ ስም ከእገታ ነፃ ወጥተዋልና እንኳን ደስ ያላችሁ!! በእስር ላይ ያላችሁም ወገኖቻችን ከኢትዮጲያ ህዝብ በላይ የሚከበር የአገር መሪ እስከሚጎበኘን ፅናቱን ይስጣችሁ ! ኢትዮጲያዊነት ዋጋው ምንም እንዲሆን ለሚታትረው መንግስታችንም በክብር የተጠየቀውን በውርደት ስለፈፀመ ‹‹መቶ ፐርሰንት የውርደት ምልክታችን ሁኖ ይኖራል››
Alex Abreham በነገራችን – ላይ

Friday, July 3, 2015

Ethiopia: Respect court rulings and release opposition members


Ethiopia: Respect court rulings and release opposition members

















Ethiopian authorities must stop harassing two men and two women linked to the opposition Semayawi (Blue) Party, and immediately release them from detention, Amnesty International said as they were expected to face fresh charges in court today in the capital Addis Ababa.

 “On five separate occasions over the course of the last 10 days, three different courts have ordered the police to release these four people,” said Michelle Kagari, Deputy Regional Director for East Africa, the Horn and Great Lakes. “Their continued detention is blatantly unlawful and in clear violation of their rights to liberty and a fair trial.”

Read More at Amnesty