Sunday, November 30, 2014

Is H&M Turning a Blind Eye to Land Grabs in Ethiopia?


Is Ethiopian police covering up the gang rape and murder of Hana Lalango?

I watched the following heart breaking report by the Ethiopian Police on EBC (formerly
called ETV) today. As a survivor of sexual assault myself, I could not help but try
to get more information and ask the following questions: 

1. Hana was recovering well after she was admitted in hospital, but suddenly she was found 
dead. The family suspect that she was poisoned in the hospital. Is the family allowed 
to have an autopsy done by an independent expert to find out the cause of her death? 

2. Why didn't the report mention that Hana was taken by her kidnappers to a shisha
 house that is frequented by government officials? 

3. Why didn't the police report mention the fact that Hana's friend who tricked her
 into going to the shisha house where the gang rape took place is still not in police 
custody? Is it because she could name the real rapists and expose other rape
 incidents that she facilitated? 

4. Why didn't the police talk about other shisha houses in several parts of Addis Ababa
that are being used to lure teenage girls and rape them? Is it because many of the 
rapists are police officers and government officials? 

Rape is common in today's Ethiopia because many of the perpetrators are powerful people.
In Hana's case, the taxi driver and a couple of other individuals may be punished, but the
real culprits will walk free. 


Friday, November 28, 2014

ሃገር ማለት – በሃብታሙ አያሌው (ሊያዩት የሚገባ).


ህወኃት ወያኔ በወልቃይት ፀገዴ ህዝብ ላይ ተጨማሪ የዘር ፍጅት ለማካሄድ እየተዘጋጀ ነው


የትግራይ ነፃ አውጭ ድርጅት ተከዜን ተሻግሮ እስካሁን በሃይል የወሰዳቸው የጎንደር ወልቃይትና ፀገዴ ቦታወች ወልቃይት፣ ሰቲት ሁመራ፣ ቃፍታ ሁመራ፣ ፀለምት፡ እና ከፀገዴ ከነበሩት ጠቅላላ 39 ቀበሌወች ውስጥ 25ቱን ቀበሌወች ወደ ትግራይ ወስዶ አንድ ወረዳ የመሰረተ ሲሆን ወደ አማራ ክልል ከፀገዴ የቀረው 14 ቀበሌ ብቻ ነው። አካባቢው በለምነቱ የታወቀና ድንግል መሬት ያለበት ሰፊ አካባቢ ሲሆን በብዛት የሚመረቱት የአዝርዕት አይነቶች ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ማሽላ፣ ሩዝ፣ ስኩኣር አገዳ፣ ፍራፍሬና አትክልት በስፋት ይመረታሉ።
በዚሁ በወልቃይት ፀገዴ አካባቢ የሚገኙና ወደ ትግራይ የተወሰዱ ትላልቅ ከተሞች ሁመራ፣ ማይካድራ፣ ማይፀብሬ፡ ዳንሻ፣ ማክሰኞ ገበያ /ንጉስ ከተማ/ና ዲቪዥን የተባሉ ከተሞች ተወስደዋል። የትግራይ ነፃ አውጭ ድርጅት ይህንኑ የመስፋፋት ስስቱን በማጠናከር በአሁኑ ሰዓት አንገረብ ወንዝን በመጠቅለል የፀገዴ ቀሪ ቀበሌወችን እና የታች አርማችሆ ለም መሬትን ለመውሰድ እየተዘጋጀ እንደሆነ ያካባቢው ጭብጦች ያስረዳሉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የወልቃይትና የፀገዴ ህዝብ አሁንም በጉልበት የተነጠቀውን የጥንት የጠዋቱን መሬት ለማስመለስና መብቱን ለማስከበር ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ሲሆን ለትግሉም መላው የኢትዮጵያን ህዝብ በተለይም የአማራ ህዝብ ከጎኑ እንዲቆም ጥሪ እያቀረበ ነው።
ይህንን የተረዳው የትግሬ ነጻ አውጭ ድርጅትም የሚያጋጥመውን የህዝብ ተቀዋውሞ ለመጨፍለቅና ያሰባቸውን ተጨማሪ መሬቶች ለመውሰድ ባካባቢው የተለያየ የፀጥታ ሃይሎችን እያደራጀና እያዘጋጀ ነው።
ከሚያደርጋቸው ዝግጅቶችም፡-
1ኛ. 120 የትግሬ ተወላጆች በልዩ ሁኔታ ተመልምለው በሁመራ ከተማ ለሁለት ወር ያክል ልዩ ስልጠና በሚስጥር ተሰጥቷቸው ስልጠናቸውንም ነሃሴ 7 2006 ዓ.ም አጠናቀዋል። የነዚህ ልዩ ሰልጣኞች ተልዕኮ በወልቃይት ፀገዴ ውስጥ ትግሬ አይደለንም አማራ ነን የሚሉትን እና መሬታችን ይመለስ የሚል ጥያቄ የሚያነሱትን እየለዩ እንዲደበደቡ እንዲገርፉ እንዲያስሩና እንዲገድሉ የተዘጋጁ ናቸው። እነዚህ ገዳይ የወያኔ ሚሊሻወች ቋሚ ደመወዝና ቀለብም የሚሰፈርላቸው ሲሆን የሚመሩትም በህወሃት ከፍተኛ መሪወች እንደሆነ ታውቁኣል።
2ኛ. የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት በወረራ የያዛቸውን የጎንደር ወልቃይት ፀገዴን መሬት አስተማማኝ በማድረግ የመስፋፋት ህልሙን እውን ለማድረግ ይረዳው ዘንደ በፀለምት ዲቪዝን ከተማ 1500 የሆኑ የትግሬ ተወላጆች ከተለያዩ የፀጥታ ተቋሞች በማውጣጣት በዚሁ ከተማ አደራጅቶና አዘጋጅቶ ለማንኛውም የአካባቢው ስራ ዝግጁ አድርጎ አስቀምጧቸዋል። እነዚህ አባላት አብዛኛወቹ የቀድሞ የህወኃት አባላት የነበሩ ሲሆኑ ከመከላከያ፣ ደህንነት፣ ፖሊስና ከትግራይ ፈጥኖ ደራሽ /ልዩ ሃይል/ ከሚባሉት የፀጥታ መዋቅሮች ተውጣጥተው የተደራጁና በተጠንቀቅ ላይ እንዲቀመጡ የተደረጉ ናቸው።
3ኛ. ይህንኑ እንቅስቃሴ ታሳቢ በማድረግ ተጨማሪ የትግራይ ልዩ ሃይልም ማዕከሉን ማይካድራና ዳንሻ አድርጎ እንዲቀመጥና ለማንኛውም ግዳጅ ዝግጁ እንዲሆን ተደርጉኣል። በተጨማሪም ተከዜን ተሻግሮ የሰፈረው የትግራይ ተወላጅ በሙሉ የጦር መሳሪያ እንዲታጠቅ ተደርጓል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በተለይም በፀገዴ ወረዳ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ግደይ አዛናው የተባለውና የዚሁ አስተዳዳሪ አባት የሆኑት የምድረ-ገበታ ቀበሌ አስተዳዳሪና የወያኔ ተቀጣሪ ካድሬ አቶ አዛናው ገብርየ በትውልዳቸው የደባርቅ ተወላጅና አማራ ቢሆኑም በጥቅም በመገዛት አማራነታቸውን የከዱና የፀገዴ ህዝብ አማራ አይደለህም አማርኛ እንዳትትናገር እያሉ በስብሰባ ሁሉ የሚቀሰቅሱና ፀገዴን ለመሸጥ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ካሉት ባንዳወች ግንባር ቀደሞቹ በመሆናቸው በአካባቢው ህዝብ ጥርስ ውስጥ መግባታቸው ታውቁል።
ሌላ በደረሰን መረጃ መሰረት ደግሞ አቶ ካሳሁን ሲሳይ የተባለ በፀገዴ ወረዳ ምድረ-ገበታ ቀበሌ ይኖር የነበረ ሰው በ1982 ዓ.ም ህወኃት በማናለብኝነት የወልቃይት ፀገዴን መሬት በሃይል ሲወስድ ከተቃወሙት ሰወች አንዱ ስለነበር፣ በወቅቱ የትግሬ ነጻ አውጭ ድርጅት ሰውየውን ይዘው ገርፈውና አስረው ሽሬ በመውሰድ ለ20 አመት ያክል ካሰሩት በኋላ በሃምሌ 2006 የፈቱት ሲሆን ሰውየው ከስር ተመልሶ ወደ ቀየው ሲመጣ “ይህ ያንተ አገር ስላልሆነ እዚህ መኖር አትችልም” ተብሎ ከተወለደበት፣ እትብቱ ከተቀበረበትና ካደገበት ቦታ በአሳዛኝ ሁኔታ እንዲባረር ተወስኖበት እንዲሰደድ ተደረጉኣል።

Thursday, November 27, 2014

በቀለ ገርባ

የሚሊዮኖች ድምፅ ቀጣይ መርሀ ግብሮች

አቶ በቀለ ገርባ
10734019_734141523337451_8980381146422839409_n
አቶ በቀለ ገርባ
ነሐሴ 21/2003 ዓ/ም ከምሠራበት ቦታ በስልክ ተጠርቼ በተለምዶ ማዕከላዊ ተብሎ ከሚጠራው የፌዴራል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ተወስጄ ከአንዲት ትንሽ ጨለማ ክፍል ውስጥ ከተወረወርኩ በኋላ በማግስቱ አራዳ ወረዳ ፍ/ቤት ቀርቤ የሃያ ስምንት ቀን የምርመራ የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆብኝ ተፈቅዶላቸው ያም ሲያልቅ እንደገና ሌላ ቀጠሮ ተጠይቆ ተፈቅዶላቸው፣ የማይመለከቱኝን ጥያቄዎች ስጠየቅና ስመልስ ቆይቼ ጥቅምት 3/2004 በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቤ የክስ ወረቀት ደርሶኝ ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተልኬ እነሆ እስከዛሬ ድረስ ዞን አንድ ቅጣት ቤት ተብላ በምትጠራው ቤት እገኛለሁ፡፡

የቀረበብኝ ክስ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 241 የተመለከተውን በመተላለፍ የአገሪቱን የፖለቲካና የግዛት አንድነት በመንካት ወንጀል ሲሆን ዝርዝሩ፡- “የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦ.ነ.ግ/ አባል በመሆን ሶሎሎ ጐልቦ ሥልጠና ወስደሃል፤ በጥር ወር 2002 ዓ/ም በአምቦ ከተማ ኦ.ነ.ግ በቅርብ ወደ አገር ውስጥ አሸንፎ ይገባል፤ ከጐኑ ቆመን በሥልጣን ላይ ያለውን መንግስት መጣል አለብን ብለህ መመሪያ ሰጥተሀል፤ በሐምሌ 2003 ዓ/ም ተማሪዎችንና ህዝቡን ለአመጽና ለብጥብጥ እንዲነሳሱ ቅስቃሳ አካሂደሀል፤ እንዲሁም በ2004 ዓ/ም በመላው ኦሮሚያ አመጽና ብጥብጥ በማስነሳት በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት መጣል አለብን በማለት ትዕዛዝ አስተላልፈሀል፤ በዚሁ ወር የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርነትህን ሽፋን በማድረግ ቢሮህ ተገኝተው የመመረቂያ ጽሁፍ ሊሰጡህ የመጡትን ተማሪዎች በሥልጣን ላይ ያለውን መንግስት በሃይል ከሥልጣን እናውርድ በማለት መመሪያ ሰጥተሀል” የሚል ነው፡፡

እነዚህ የቀረቡብኝ ክሶች ፈጽሞ የሀሰት ውንጀላዎች መሆናቸውን ለማስረዳት በመጀመሪያ ደረጃ ትጥቅ ትግልና ሰላማዊ ትግልን አስመልክቶ ያለኝን አቋምና እምነት ባጭሩ ከገለጽኩ በኋላ በቀረቡብኝ ምስክሮችና የሠነድ ማስረጃ ላይ ያሉትን እውነታዎች አቅርቤ በአጭሩ የማጠቃለያ ሀሳብ እደመድማለሁ፡፡

የግሪክን ብሔራዊ ህልውና የተፈታተነ ”ሶቨሪን ቦንድ” ለኢትዮጵያ እንዴት ይሰራል?

ministry of finance
ኢትዮጵያ ከእዚህ በፊት ከመንግሥታት፣አህጉራዊ ወይም ዓለም ዓቀፍ የገንዘብ ተቋማት ብድር ወስዳለች።አሁን ያለባት የብድር መጠን ከ20 ቢልዮን ዶላር ወይንም ከ400 ቢልዮን ብር በላይ መሆኑ ይታወቃል።ወደ ”ሶቨሪን ቦንድ” እንድትገባ በዝግ ምክርቤት ወሰነ የተባለው የብድር አይነት ግን ኢትዮጵያ ከግል አበዳሪዎች ሁሉ በደላሎች ብድር እየፈለገች እንድትበደር የሚያደርግ፣በሙስና ለተሰነገ ሀገር ፈፅሞ የማይመከር ነው።ለመሆኑ የሶቨርን ቦንድ ምን ማለት ነው? ”ኢንቨስቶፕድያ እንዲህ ይገልፀዋል።
”ሶቨሪን ቦንድ” ማለት በመንግሥታት በውጭ ምንዛሪ የሚቀርብ የብድር ዋስትና ሲሆን የውጭ ምንዛሪው በጠንካራ አለም አቀፍ ገንዘብ (ሃርድ ከረንሲ) የተደገፈ ነገር ግን ለቦንድ ያዥው የበለጠ አደጋ ያለው ” ይላል
”DEFINITION OF ‘SOVEREIGN BOND’
A debt security issued by a national government within a given country and denominated in a foreign currency. The foreign currency used will most likely be a hard currency, and may represent significantly more risk to the bondholder.” www.Investopedia.com

Best speech Eng.Yilekal



ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚደረግ ደባ፣ ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

Nov 26, 2014
ለአራት አስርት ዓመታት እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው እና በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ከህዝብ ፍላጎት ውጭ በኃይል በስልጣን ወንበር ላይ ተፈናጥጦ የሚገኘው የወሮበላ የማፊያ ቡድን ኢትዮጵያን ለማጥፋት ቀጣይነት ያለው እና የማያቋርጥ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የባህል ጦርነት በመክፈት ዕቅድ አውጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ የህወሀት ኢትዮጵያን የማጥፋት ተልዕኮው እና ፍልስፍናው የተመሰረተው በተወሰኑ የአፈጻጸም ስልቶች፣ ፖሊሲዎች፣ የድርጊት መርሀ ግብሮች እና ተሞክሮዎች ላይ ሲሆን በዋናነት የሚከተሉትን የአፈጻጸም ስልቶች ያካትታል፣ 1ኛ) የኢትዮጵያውያንን/ትን ብሄራዊ ማንነት በጠባብ እና በጎሳዊ አመላካከት ተክቶ በመከፋፈል ኢትዮጵያውያን/ት ያሏቸውን የማህበራዊ የጋራ ልምዶች፣ የህዝቡን የተከበሩ እሴቶች፣ እምነቶች እና ልማዶች ፍጹም በሆነ መልኩ እንዲወገዱ አበርትቶ መስራት፣ 2ኛ) የተለያዩ ዕኩይ የተግባር ስልቶችን እና ዕቅዶችን በማዘጋጀት ሀገሪቱን መከፋፈል፣ መሸጥ፣ መገንጠል እና መገነጣጠል፣ የወያኔ ኢትዮጵያን የማጥፋት ፍልስፍና እና ዕቅዶች ዓላማ አድርገው የተነሱት ኢትዮጵያ ተብላ የምትጠራዋን የአንጸባራቂ ታሪክ ባለቤት የሆነች ሀገር በማስወገድ ጭራቃዊነት በሆነ መልኩ በተጸነሱ፣ ለእኩይ ምግባር ፍጻሜው በጥንቃቄ በታቀዱ እና እነዚህን መሰሪ ዕቅዶች ስልታዊ በሆነ መልኩ ተግባራዊ በማድረግ በመጨረሻ በወያኔ ምናብ የተፈበረከች በጎሳ ተበጣጥሳ እና ተጣማ በተሰራች ደካማ ሀገር ለመተካት ነው፡፡ ወያኔ ኢትዮጵያን የማጥፋት ተልዕኮውን እ.ኤ.አ ከ1991 ጀምሮ በይፋ እና ግልጽ በሆነ መልኩ መተግበር ጀመረ፡፡   

Tuesday, November 25, 2014

በለገጣፎ ከተማ ከ32,000 ሺህ በላይ ዜጐች ቤት አልባ ሊሆኑ ነው

(ፍኖተ ነፃነት) የአዲስ አበባ ተዋሳኝ በሆነው ለገጣፎ ከተማ ከ3,000 ሺህ በላይ ቤቶች እንዲፈርሱ በመወሰኑ ከ32,000 ሺህ በላይ ዜጐች ቤት አልባ ሊሆኑ እንደሆነ ነዋሪዎቹ ገለፁ፡፡
legetafo Addis ababa






















ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ለ12 ዓመታት በአካባቢው መኖሪያ ቀልሰው ኖረዋል፡፡ ሆኖም “የከተማ ሰው ወሮናል” የሚል ተቃውሞ በገበሬው እንዲነሳ ያደረጉ የከተማው ባለሥልጣኖች በ2 ቀናት ውስጥ ቤታችን ሊያፈርሱ ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ የካ ሰዴን ወረዳ የሚገኙት የጉራ፣ሰፈራ፣ድሬ፣ ዳሌ እና ቀርሳ የሚባሉ አካባቢዎች ውስጥ የሚገኙ ወደ 3000 ሺህ የሚጠጉ ቤቶች እንዲፈርሱ ምልክት ተደርጎባቸዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ቅዳሜ ህዳር 13 ቀን 2007ዓ.ም በከተማው በመሰባሰብ ተቃውሞአቸውን አሰምተዋል፡፡ በነጋታው እሁድ ዕለትም ከ1000 በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች በመሰባሰብ ባጋጠማቸው አደጋ ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የነዋሪዎቹን ችግር ለማዳመጥ ፈቃደኛ ያልሆኑት የከተማው የመንግስት ባለስልጣናት ግን በቅዳሜው በስብሰባው ላይ ባለመገኘታቸው ነዋሪዎቹ በነጋታው እሁድ ከ1000 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች በወረዳው ጽ/ቤት በመገኘት ተቃውሞ አሰምተዋል፡፡ ሰኞ ህዳር 15 ቀን 2007 ዓ.ም በድጋሚ በመሰባሰብ 10 ተወካዮቻቸውን ወደ 4 ኪሎ ፓርላማ መላካቸውን በስፍራው የተገኘው የፍኖተ ነፃነት ዘጋቢ አረጋግጧል ፡፡
Link;-http://www.zehabesha.com/amharic/archives/36559

ወጣቱ ፖለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው የተናገረው

በግልፅ ከተቀመጠው አላማዬ ውጪ ሌላ የተደበቀ አላማ እስከሌለኝ የትም ቦታ ንፁህ አዕምሮ አለኝ ፡፡ንፁህ አዕምር ይዤ እኖራለሁ የመጨረሻው አማራጭ ወደ እስር ቤት መወርወር ሊሆን ይችላል እድል ፈንታችን ይሔ ሊሆን ይችላል ፡፡ይሔ ለኛ የተለየ አዲስ ነገር አይደለም በሰው ሁሉ ላይ ከደረሰው በእናንተ ላይ የደረሰ ምንም ነገር የለም ይላልና መፅሀፍ እኔም የተለየ ነገር ሊደርስብኝ አይችልም ፡፡ከቀድሞም ጀምሮ ኢትዮጵያ እንደዚህ ልጆቿን ስትበላ የኖረች ሀገር ናት፡፡አባቶቻችንም በተረት ይሉታል‹‹ኢትዮጵያ ሀገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ››እንስራ ለዚች ሀገር ባልን እንደዚህ አይነት ፈተናና መከራዎች መጋረጣቸው ያሳዝናል፡፡ቢያንስ ትውልዱ እንደዚህ አይነት ፈተና እንዳይገጥመው፤ልጄ እንዲህ አይነት ፈተና እንዳይገጥማት እኔ ይህንን ፈተና ተጋፍጬ ማለፍ አለብኝ፡፡ግን ሁሌም ዲሞክራሲያዊ መሆን አለብኝ ብዬ አምናለሁ ፡፡ፀረ ዲሞክራሲያዊ የሆነ አስተሳሰብን በፀረ ዲሞክራሲያዊ መንገድ መፍታት አይቻልም፡፡ፀረ ዲሞክራሲያዊ የሆነን አስተሳሰብ መፍታት የሚቻለው በዲሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ ነው፡፡በዲሞክራሲያዊ መንገድ መፍታት እንደሚቻል ደግሞ ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡

Monday, November 24, 2014

ሰለ ሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ፤ ለሰማዩ አምላኬ ጸሎት አደርሳለሁ…!

ሰማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች ዘጠኝ ፓርቲዎ በመተባበር ”ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ” በሚል ቀጣዩ ምርጫ ነጻ እንዲሆን ምርጫው ብቻም ሳይሆን በኢትዮጵያ ምድር የሰው ልጆች ነጻ እንዲሆኑ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከህዝብ ጋር በመሆን ድምጻቸውን ሊያሰሙ የክንውን ቅደም ተከትሉን በቅርቡ ይፋ አድርገዋል። ይደረጋሉ ተብለው ከሚጠበቁት የ10484897_675825339202040_7611881303839978882_nሰላማዊ ተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ትልቁ መርሃ ግብር የሚሆነው ህዳር ሃያ ሰባት እና ሃያ ስምንት ሊደረግ የታሰበው የሃያ አራት ሰዓታት /የአዳር/ የአደባባይ ተቃውሞ ነው።
ከእርሱ በፊትም የፊታችን እሁድ በአዋሬ ቤልኤር ኳስ ሜዳ ላይ ከሚደረገው የአደባባይ ሰብሰባ በፊትም በጥቅሉ ከሁሉም መርሃ ግብሮች በፊት እነ ሰማያዊ ሁላችንም በየእምነታችን ለሰማዩ አምላክ ”አደራ ጎፍታ” ብለን እንድንጸልይ ጠይቀውናል… ታድያ አሁን ባለሁበት ሁኔታ ለአደባባይ ተቃውሞውም ሆነ ለስብሰባው መድረስ ባልችል እንኳ እንደሚከተለው ለምን አልጸልይም… ብዬ አስብኩ…
አደራህን ጎፍታ
አደራህን ጌታ
ከባለ ሰይፎቹ ፊት
ሰልፍ ልንወጣ ነው ጥበቃህ ይበርታ
ብዙ ስንቅ ብዙ ትጥቅ እጅግ ያደራጁ
በስልጣን ወንበር ላይ ጎልምሰው ያረጁ
ስልጣን ብርጭቆ ውስጥ ስኳር በዝቶባቸው
እጅጉን ጣፍጧቸው
ስልጣን ብርጭቆ ውስጥ ብቅል በስቶባቸው
እጅግ አስክሯቸው
ቢጠጡት ቢጠጡት አልበቃም ያላቸው…
ምን ያደርጉን እንደሁ አናውቀውምና
ለኛም ብርታት ስጠን ለነርሱም ልቦና
አደራህን ጎፍታ
አደራህን ጌታ
ከባለ ሰይፎች ፊት
ሰልፍ ልንወጣ ነው ጥበቃህ ይበርታ….
(ይቺን ነገር፤ የግጥምን አድባር ተለማምነን ካረዘምናት እና ተስፋ ሰጪ ሆና ከተገኘች በሌላም መስኮት ይዘናት እንከሰት ይሆናል…!)

ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት በቁጥር ‘S/2014/727’፣ በ ‘October 13, 20141 የወጣውን ሪፖርት በተመለከታል፤ ከሞረሽ ወገኔ ዐማራ የሲቪክ ድርጅት የተሰጠ መልስ

November 22, 2014
moresh-logo
ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት
Security Council Report One Dag Hammarskjöld Plaza 885 Second Avenue at 48th Street, 21st Floor New York, NY 10017
Telephone: 212-759-9429 Fax: 212-759-4038 Email: contact@securitycouncilreport.org
ኒውዮርክ፤
ከሞረሽ ወገኔ ዐማራ የሲቪክ ድርጅት
ሲልቨር ስፕሪንግ፣ ሜሪላንድ 20910
ዩ.ኤስ. አሜሪካ

ጉዳዩ፦ በቁጥር ‘S/2014/727’፣ በ ‘October 13, 20141 የወጣውን ሪፖርት ይመለከታል፤
  1. ሞረሽ ወገኔ ዐማራ የሲቪክ ድርጅት (ሞወዐድ)፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚኖሩት ፹፩ (ሰማንያ አንድ) ያህል ነገዶች እና ጎሣዎች (ብሔር/ብሔረሰቦች) መካከል በቁጥሩ ከጠቅላላው የአገሪቱ ሕዝብ ፴፭(ሰላሣ አምሥት) በመቶ ያህሉን ለሚይዘው እና ለሚደርስበት በደል የሚሟገትለት ቋሚ ጠበቃ ለሌለው የዐማራው ነገድ (ብሔር) ድምፅ ለመሆን የተቋቋመ የሲቪክ ድርጅት ነው። ድርጅቱ ከመስከረም ወር ፪ሺህ፭ ዓም (Sep 2012) ጀምሮ በተባበሩት የአሜሪካ ግዛቶች፣ በሜሪላንድ ግዛት ሕጋዊነት አግኝቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። ይህን ደብዳቤ ለተከበረው የፀጥታው ጥበቃ ምክር ቤት ለመጻፍ ያነሣሣንም፣ ከላይ በርዕሰ-ጉዳዩ ሥር በተጠቀሰው መግለጫ በገፅ ፴፩(ሰላሣ አንድ)፣ በአንቀፅ ፸፰(ሰባ ስምንት) የተገለፁት አረፍተነገሮች ፍፁም ከተሳሳተ መረጃ የተነሱ እና መሠረት የሌላቸው በመሆናቸው፣ በዘገባው የቀረቡትን አብዛኞቹን ዝርዝር ጉዳዮች ወደተዛባ አጠቃላይ ድምዳሜ ወስዷል የሚል ዕምነት ስላለን ነው።
  2. በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የትግሬ-ወያኔ (ሕወሓት) አገዛዝ የዐማራን ነገድ በአጠቃላይ በዘር ጠላትን ፈርጆ በመተዳደሪያ መርኃግብሩ ላይ ያሠፈረ ድርጅት ነው (አባሪ ፩ን ይመልከቱ)። ይህ ድርጅት ለ፲፯ (አሥራሰባት) ዓመታት በሽፍትነት፣ ለ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት ደግሞ በሥልጣን ላይ በቆየባቸው ጊዜያት በዐማራው ሕዝብ ላይ ያደረሰው የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት የወንጀል መጠን ሊስተካከለው የሚችለው በ፪ኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የናዚ ጀርመኖች በአይሁዳውያን ላይ የፈፀሙት ‘Holocaust’ ብቻ ነው። የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ዓለም በምትገኝበት ለሰብአዊነት ትልቅ ከበሬታ በተሰጠበት ዘመን፣ የወያኔ አገዛዝ ዐማራን በደመኛ ጠላትነት ፈርጆ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ሁሉ አቀፍ የጥፋት ዘመቻ በከፈተበትና እያንዳንዱን ተቃዋሚውን «ዐማራ ነው» እያለ በሚያሳድድበት ወቅት፤ ‘ግንቦት7’ ተብሎ የሚጠራው ድርጅት ዋና መሪዎች የዐማራው ሊሂቃን ናቸው ተብሎ በሪፖርቱ በዋናነት መጠቀሱ ነገዱን ለማጥፋት ቆርጦ ለተነሳው አገዛዝ «ድርጊትህ ትክክል ነው፣ ቀጥል ግፋበት» የሚል እንደምታ የሚያስተላልፍ መልዕክት የያዘ ሆኖ ስላገኘነው ድርጊቱ ከማሳሰብ አልፎ አሳዝኖናል።  ……  (ሙሉውን ከዚህ ላይ ያንብቡ, pdf )


ሀና ላላንጎ የተደፈረችው ሺሻ ቤት ውስጥ ነበር! ፖሊስም ተጠያቂ ነው!

ለዚህ እና ለሌሎችም ጥያቄዎች ምላሽ የምናገኘው ደግሞ ከውስጥ አዋቂ ምንጭ ነው:: ይህ ውስጥ አዋቂ ሃና የተደፈረችው ያለ ፍላጎቷ ሺሻ ቤት ተወስዳ መሆኑን በዝርዝር ያስረዳል:: ይህ የሃና ጉዳይ በጣም የብዙ ሺህ እህቶቻችን ጉዳይ መሆኑንም ያብራራል:: በተለይም እነዚህ ሺሻ ቤቶች በትምህርት ቤት አቅራቢያ የሚገኙ በመሆናቸው ለወጣት ተማሪዎች መጥፊያ እየሆኑ ነው:: በውጭ አገር በትምህርት ቤት እና በአምልኮ ቦታዎች አቅራቢያ የመጠጥ እና የንዲህ አይነት ነውረኛ ድርጊት መፈጸሚያ ቦታዎች እንዳይኖሩ አጥብቆ ይከለክላል:: በአገራችን ግን እነዚህ ሺሻ ቤቶች በትምህርት ቤት አቅራቢያ እየተከፈቱ ለወጣቶች መጥፊያ እንደሆኑ የሃና ጉዳይ አንዱ ምስክር ነው::
hanna

ይህን ጽሁፍ አንብበው ሲጨርሱ “ፍትህ ለሃና” ከሚለው ዘመቻ በተጨማሪ; ሺሻ ቤቶች ከትምህርት ቤት አቅራቢያ እንዲነሱ የሚጠይቅ አዲስ ዘመቻ መከፈት ያለበት ይመስለናል:: “ፍትህ ለሃና” ካልን’ ፖሊስ ጭምር በሃና ሞት ምክንያት ከተጠያቂነት መዳን የለበትም:: “የፖሊሶቹስ ጥፋት ምን ነበር?” ካላቹህ ይህንን ጽሁፍ በሙሉ ማንበብ ይኖርባችኋል:: ለማንኛውም አንዳንድ ማስተካከያ አድርገን ያቀረብንላችሁ የውስጥ አዋቂው (ሰይፈዲን ሙሳ) ዘገባ ከዚህ ቀጥሎ ቀርቧል::

Sunday, November 23, 2014

“ምስጢር ካወጣህ ቤተሰቦችህን እንፈጃቸዋለን”

                  “ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል”
“የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል”
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ በዝዋይ እስር ቤት ለወራት ስቃይ የተፈፀመበት
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ይባላል፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ አዳማ/ናዝሬት አድጎ፣ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት የመንግስት ደህንነት ሀይሎች ተያዞ ለ23 ወር በዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ከወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ጋር ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉን፡፡
ፍኖተ ነፃነት፡- ማን ነበር ያሰረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በማለዳ ቤቴ ተንኳኳ፤ ተነስቼ ከፈትኩኝ፡፡ የማላውቃቸው ሰዎች ናቸው፡፡ “ና ውጣ፤ ልብስህን ለብሰህ ውጣ” አሉኝ፡፡ እኔ እናቴ ሞታ ሊያረዱኝ የመጡ መስሎኝ “ምነው ቤተሰብ ደህና አደለም? የተፈጠረ ችግር አለ?” አልኳቸው “ዝም ብለህ ናውጣ” አሉኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩኝና ወጣሁ፤ አንቀው መኪና ውስጥ ከተው ወደ ማዕከላዊ ወሰዱኝና 3 ወር አሰሩኝ ከዛም አንድ አመት ከ8 ወር ዝዋይ ማረሚያ ቤት፡፡

ከ400 በላይ ህዝብ የተፈናቀለበት መሬት በሙስና ተቸበቸበ

ኀዳር ፲፩(አስራ አንድቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-በደቡብ ወሎ ዞን በኮምቦልቻ ወረዳ ቀበሌ 11 በተለምዶ ጋሪሳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ይኖሩ የነበሩ 470 ሰዎች ቦታው ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል ተብሎ ሰብአዊ መብታቸው ተጥሶ እንዲፈናቀሉ ከተደረገ በሁዋላ፣ በካሬ ሜትር 1 ብር ከ46 ሳንቲም መሬታቸው እንዲጨጥ ተደርጓል።
ጉዳዩ የህዝብ መነጋገሪያ ሆኖ ከቆየ በሁዋላ ሰሞኑን ከህዝቡ እየጨመረ የመጣውን ግፊት ተከትሎ በተደረገ ህዝባዊና የካቢኔ አባላት ስብሰባ፣ የወረዳው አዛዦች ከተፈናቃዩ ደሃ ህዝብ የወሰዱትን መሬት በሙስና መቸብቸባቸውን እርስ በርስ እየተገላለጡ ይፋ አድርገዋል።
የወረዳው ላይዘን ኦፊሰር አቶ ሃብቶም የተባሉ ግለሰብ፣ አስተዳዳሪውን አቶ አበራ አበረን በአዲስ አበባና በባህርዳር መሬት ገዝተው ቤት መስራታቸውንና ቡልዶዘሮችን ገዝተው እያከራዩ መሆኑን ሲያጋልጡ፣ ምክትል ከንቲባው ደግሞ በባንክ ሂሳባቸው 8 ሚሊዮን ብር እንደተገኘባቸውና  በተለያዩ አካባቢዎች ቤቶችን
መገንባታቸውን አጋልጠዋል። አጋላጩ አቶ ሀብቶምም እራሳቻው በከተማዋ ሁለት ቦታ ገዝተው ቤት መስራታቸውና መቀሌ ላይ ተጨማሪ ቦታ መግዛታቸው በሌሎች ባልደረቦቻቸው ተጋልጧል።
ሶስቱም ባለስልጣኖች ለጊዜው ከስራቸው ቢታገዱም እስካሁን የተወሰደባቸው እርምጃ የለም። አንዳንድ ተፈናቃይ አርሶደአሮች  አቤቱታ ቢያቀርቡም ሰሚ በማጣታቸው ለስደትና ለረሃብ መዳረጋቸውን ለኢሳት ገልጸዋል ። ሰዎቹ ከስራ ቢሰናበቱም ወደ ሌላ ቦታ ተዛውረው መስራታቸው አይቀርም የሚል  ጥርጣሬ እንዳላቸውም አክለዋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በደቡብ ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ ከ100 በላይ አርሶደሮች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። አርሶ አደሮቹ የመሬት ዋስትና ወረቀት እንዲሰጣችሁ በነፍስ ወከፍ 4 ሺ 500 ብር ክፈሉ ተብለው የተጠየቁ ቢሆንም፣ እነርሱ ግን እስከዛሬ ግብር እየከፈልን ኖረናል፣ አሁን ተጨማሪ አንከፍልም በማለት ተቃውመዋል። ይህ ተከትሎ መሬታቸውን እየተቀሙ ይዞታቸው ለኢንቨስተር በሚል ሽፋን እየተቸበቸበ ነው። አብዛኞቹ ባለስልጣኖች ከኢንቨስተሮች ጋር አክሲዎን እንዳላቸው የገለጹት መንጮች በአካባቢው የሚታየው ተደጋጋሚ ግጭት ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን  ይናገራሉ።

Saturday, November 22, 2014

ኢህአዴግ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ለማሰር መዘጋጀቱ ታወቀ • የኢህአዴግ አመራሮች መካከል ልዩነት ተፈጥሯል

ነገረ ኢትዮጵያ) ገዥው ፓርቲ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን ለማሰር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ታማኝ ምንጮች ገለጹ፡፡ ሰሞኑን የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ባደረጉት ስብሰባ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃልን ወይንስ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን ማሰር ያዋጣል በሚል ልዩነት እንደተፈጠረ የገለጹት ምንጮቻችን በስተመጨረሻም የኢንጅነር ይልቃል መታሰር ትኩረት የሚስብ በመሆኑ ንቁ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን ማሰር አዋጭ ነው የሚለው ቡድን ተደማጭነት እንዳገኘ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
blue party 2

በተመሳሳይ የሰማያዊና ሌሎች ፓርቲዎች አመራሮችን ‹‹ከኢሳት ጋር ግንኙነት ያደርጋሉ›› በሚል በሽብር ስም ለመክሰስ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችንም ሆነ ሌሎችን ‹‹ከኢሳት ጋር ግንኙነት አላቸው›› በሚል ይከሰሳሉ የተባሉት እስከህዳር ወር መጨረሻ ሊታሰሩ ይችላሉ ሲሉ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል በዚሁ ስብሰባ ኢንጅነር ይልቃል ወይንም ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን በማሰር ከተፈጠረው ልዩነት በተጨማሪ አመራሮችን በተለያዩ ሰበቦች ለማሰር በተዘጋጀውና ‹‹በዚህ መንገድ መሄዱ እስከመቼ ያዋጣናል?›› የሚሉ ጥያቄ በሚያነሱ ከፍተኛ የኢህአዴግ አመራሮች ልዩነት መፈጠሩንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም ባሻገር በሌሎች የፓርቲው አካሄዶች ላይ ልዩነት በመፈጠሩ ፓርቲው ውስጥ አደጋ ተፈጥሯል ያሉት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች በአቶ አባይ ፀሐዬ የሚመራ ቡድን ‹‹ልዩነታችን ቢያንስ እስከ ምርጫው ድረስ ማቻቻል አለብን›› በሚል በሁለቱ ቡድን መካከል ያለውን ልዩነት ለመፍታት እየጣረ ነው ብለዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች 8 ፓርቲዎች ጋር በመተባበር የአዳር ሰልፍን ጨምሮ የአንድ ወር መርሃ ግብር ቀርጾ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን የወሩ የመጀመሪያ መርሃ ግብር የሆነው የአደባባይ ስብሰባ ለማድረግ ሲቀሰቅሱ የተገኙ የፓርቲው አራት አመራሮች መታሰራቸው ይታወቃል፡

“ኢቦላ” – ለድሆች የቀረበ የወረርሽኝ ኢንቨስትመንት!?

“ማምከን፣ ማኮላሸት” የህወሃት “ስጦታ”
በተለያዩ ወቅቶች የሰውን ልጅ ከእንስሳ በማሳነስ የተፈጸሙ ወንጀሎች ስለመኖራቸው መረጃዎች ይወጣሉ። በቤተ ሙከራ ውስጥ የሚፈበረኩትና ሆን ተብለው እንዲሰራጩ የሚደረጉት የበሽታ መነሻዎች የክቡር ሰው ልጆችን ህይወት በሚዘገንን ሁኔታአራግፈውታል። አባት፣ እናት፣ ልጅ፣ የልጅ ልጅ፣ አልፎ ተርፎ ትውልድ … የሰው ልጅ በሽታ ኢንቨስት ተደርጎበት፣ የሕዝብ ብዛት መቀነሻና የባዮሎጂካል ጦር መሣሪያ መመራመሪያ ተደርጓል፣ አሁንም እየተደረገ ነው፤ የበሽታ ማምከኛ መሞከሪያና ማፈላለጊያ ሆኖ ኖሯል። ዛሬም እየኖረ ነው። የሌላውን አገር ሕዝብ ከህይወት በታች፤ የራሳቸውን ግን ድርብ ህይወት እንዳላቸው አድርገው የሚቆጥሩት ምዕራባውያን እንደመልካቸው ለማሳመር የሚሞክሩት ታሪካቸው ለማመን የሚያስቸግር እና ለመቀበል የሚከብድ ፍትሕ ያልተሰጠባቸው “ወንጀሎች” አካሂደዋል፤ አሁንም በረቀቀ መንገድ እያካሄዱ ነው፡፡ በዚሁ መነሻና እሳቤ ይመስላል ኢቦላን ለድሆች የቀረበ የወረርሽኝ ኢንቨስትመንት እንደሆነ አድርገው ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ እየተቹ ያሉት።
አጀንዳው ሰፊና ቢጎለጉሉት የማያልቅ፣ ዙሪያ ገባው ሁሉ መርገምት የሆነ ወንጀል ነው። በእኛም አገር አማራው ህዝብ ላይ የዘር ፍሬን የማምከን ጸያፍ ወንጀል ስለመፈጸሙ ማስረጃ ቀርቧል። ሰለባዎች አደባባይ ወጥተው ተናግረዋል። ድርጊቱ የተፈጸመው ቴድሮስ አድሃኖም የጤና ጥበቃ ሚኒስትር እያሉ መሆኑ እየታወቀ በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለምአቀፍ ደረጃ (“ተልዕኮ” አስፈጻሚ በመሆናቸው ይመስላል) ተሸላሚና ተሿሚ ለመሆን በቅተዋል። ለአማራው እንቆረቆራለን የሚሉ “የሰው ብሎች” ድርጊቱን ተቀብለው ባቃጣሪነት ለመዝለቅ መወሰናቸው ከተፈጸመው ወንጀል በላይ የሚዘገንን ይሆናል።
የአንድ መንደር ህዝብ በባዮሎጂካል መሳሪያ ተመሳጥሮ ማስጨፍጨፉ የተመሰከረበት ህወሃት ቢታጠበው የማይጸዳለት ግፍ የሚፈጽምበት የአማራ ህዝብ እንዲመክን መደረጉን የሚያሳየው ቪዲዮ ወደታች ስለሚገኝ ለአንባቢ ዕይታ ቀርቧል፡፡

Wednesday, November 19, 2014

የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች!

የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት አንዱ አካል የሆነው የህሊና እስረኞችን የሶሻል ሚዲያ ንቅናቄ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ዘመቻ ሲሆን ከሚቀጥለው ከእሁድ ከህዳር 14 እስከ 20/2007 የሚቀጥል ፕሮግራም ነው። በዚህ ዘመቻ ሚሊዮኖች የፖለቲካ ይሳተፋሉ፤ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፣ ተገቢ የሆነ አያያዝ እንዲኖራቸው፤ በሰላማዊ መንገድ የሚታሉትን ማሰርና ማዋከብ እንዲቆም ድምፃቸውን ያሰማሉ፤

ዘመቻው ለመንግስት ባለስልጣናት፣ ለመንግስት መስሪያቤቶች፣ ኤምባሲዎች፣ ለታዋቂ ግለሰቦች፣ ለአለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ተሟጓች ተቋማት፣ ለተለያዩ ሚዲያዎች፣ በE‐mail በsms፣ በinbox ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የህሊና እስረኞች አያያዝና የእስር ሁኔታ፣ የታሳሪዎች ማንነትና አሁን የሚገኙበት ሁኔታ ወዘተ በመግለፅ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ማድረግ ነው።
በዚህ ዘመቻ የፖለቲካ አመለካከት፣ ቋንቋ ዘርና ሀይማኖት ሳይለየን ሁላችንም መሳተፍና ድምፃችንን ማሰማት ይኖርብናል። ሳምንቱን ሙሉ ሁሉም የህሊና እስረኞች የሚመለከት ቅስቀሳና ዘመቻ ሲኖር በተለየ ሁኔታ ደግሞ በየቀኑ የሚታወሱ የህሊና እስረኞች ይኖራሉ፤ እነርሱም የሚከተሉት ናቸው።
እሁድ፦ አንዷለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮነን እና ሌሎች የአንድነት አባላት
ሰኛ፦ እስክንድር ነጋ እና ርዕዮት አለሙ
ማክሰኛ፦ አብርሃ ደስታ የሽዋስ አሰፋ እና ሀብታሙ አያሌው እና ዳንኤል ሽበሺ
ሮብ፦ በቀለ ገርባ፣ ኦልባና ሌሊሳና ሌሎች የኦሮሞ ታሳሪዎች
ሀሙስ፦ ተመስገን ደሳለኝ እና ውብሸት ታዬ
ዓርብ፦ የሞስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ እነአቡበከር
ቅዳሜ፦ ዞን ዘጠኝ
የሳምንቱ መሪ መፈክር የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች!
Millions of voice for prisoners of conscience! የሚል ሲሆን በየቀኑ በተለየ ሁኔታ የሚቀነቀኑት መፈክሮች ደግሞ የሚከተሉት ናቸው
እሁድ ማክሰኞ እና ሮብ የሚኖሩት መሪ መፈክሮች፦
በሽብርተኝነት ሽፋን ሰላማዊ ታጋዮች ማሰር ይቁም
የህሊና እስረኞች እንጂ አሸባሪዎች አይደሉም
የሽብር አዋጁ ይሰረዝ
መንግስታዊ ሽበራ ይቁም
የዜጎች በሰላማዊ መንገድ የመደራጀት መብት ይከበር
ሰኞ እና ሀሙስ የሚኖሩት መሪ መፈክሮች፦
Because I am Journalist!
ጋዜጠኞች ማሰርና ማሳድድ ይቁም
ሀሳብን የመግለፅ ነፃነት ይከበር
ዓርብ ዕለት የሚኖሩ መሪ መፈክሮች፦
የኃይማኖት ነፃነት ይከበር
የሞስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎች ይፈቱ
መንግስት በማህብረ ቁዱሳን ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ ያቁም
መንግስት በኃይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ አይገባም የሚለው የህገ መንግስቱ ድንጋጌ ይከበር
ቅዳሜ ዕለት የሚኖሩ መሪ መፈክሮች፦
ሰብአዊ መብት በኢትዮጵያ ይከበር
Blogging Is Not A Crime
ሀሳበን የመግለፅ መብት ይከበር
እንደአስፈላጊነቱ ሌሎችም መፈክሮች ይኖራሉ።

Monday, November 17, 2014

London man Andy Tsege faces death penalty in Ethiopia

he family of a north London man who is facing the death penalty in Ethiopia has said the government should be doing more to help get him home. 
Andy Tsege, from Islington, who opposes the Ethiopian authorities, was seized in June and has been in solitary confinement ever since, his family says.
The Foreign Office says he is not being held "illegally".
BBC London's Charlotte Franks spoke to Mr Tsege's partner Yemi Hailemariam, Maya Foa from human rights organisation Reprieve, and Andy's sister Bezu Tsege.

Sunday, November 16, 2014

የተወሰደው እርምጃ የስርዓቱን ፍርሃት ደረጃ እንደሚያሳይ ኢ/ር ይልቃል ገለጹ




9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩትን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል መበተኑ የስርዓቱ የፍርሃት ደረጃ ጫፍ መድረሱን ያሳያል ሲሉ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ 

ኢንጅነር ይልቃል በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ ከአሁን ቀደም እንደሚያደርገው ለምን እስከመጨረሻው አንበተንም አላላችሁም? ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ‹‹የአንድ ወር መርሃ ግብር አውጥተናል፡፡ ምርጫው ነጻና ፍትሓዊ እስኪሆን ድረስ የነጻነት ትግሉ የሚቀጥል ነው፡፡ በአራት ኪሎ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ጠርተን ልናነጋግር በሞከርንበት ወቅት ብዙ እስርና ደብደባ ተፈጽሟል፡፡ ከዚህ የስርዓቱ ፍርሃት አንጻር ገና በመጀመሪያው ስራችን ወደኃይል እንዲገባ አልፈለግንም፡፡ ለሚቀጥሉት ስራዎቻችን ስንል ነው፡፡ ለሚቀጥለው ያንን በሚመጥን ደረጃ መዘጋጀት አለብን፡፡›› ብለዋል፡፡ 

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት አክለውም ‹‹እኛ ዛሬ የአራት ኪሎን አካባቢ ሰዎች ነው የጠራነው፡፡ በዚህ ደረጃ ፈርተው ይህን ስብሰባ ያግዳሉ ብሎ ለመገመት ይከብዳል፡፡ ድሮውንም የሌላቸው የህዝብ ድጋፍ ጭራሹን እንደተሟጠ ነው የሚያሳየው፡፡ ትንሹም ነገር ለስልጣናቸው አስጊ ነው ብለው ማሰባቸው የፍርሃት ደረጃቸው ጫፍ እንደደረሰ ያሳያል፡፡›› ብለዋል፡፡

Health official orders the burning of Ebola patients in western Ethiopia, secret letter reveals


Saturday, November 15, 2014

አማራ፣ ኦሮሞ፣ ስብአዊ መብቶችና ድርጅቶቻቸው፣ ተጠንቀቅ አማራ! ከቦጋለ ካሳዬ

አማራ፣ ኦሮሞ፣ ስብአዊ መብቶችና ድርጅቶቻቸው
amara
የደላቸው… የሰው ልጅ ይቅር፤ ማንኛውም ህመም ሊሰማው የሚችል ፍጡር አይጠቃ! አይገደል! ብለው እሪ! እሪ! ይላሉ። ያነባሉ። እንቅልፍ አይወስዳቸውም። የሌሎች ስቃዮች እነርሱንም ያስቃያቸዋል።
አንዴ ተማሪ እያለን የደብረ-ብርሃንን የብርድ ልብስ ፋብሪካ ልንጎበኝ ሄድን። አስተማሪያችን ፕሮፌሰር ፓንዲታ የሚባል ህንድ ነበር። ለምሳችን ስጋ ያለበት ሳንዱውች ተዘጋጅቶአል። የደብረብርሃን ብርድ ለጠኔ ዳርጎን ነበርና ሰፍ ብለን ሳንዱቻችንን መግመጥ ጀመርን። አስተማሪያችን ግን ከንፈሩ ደርቆ አይን አይናችንን ያየናል። ለመብላት ፈልጎአል። “ለምን አትበላም?” ብለን ብንጠይቀው፤ “ስጋ አልበላም። እምነቴ ማንኛውንም ፍጡር አትግደል ይላል።” ብሎን እርፍ!
በሆላንድ የእንሳስት መብት ተሙዋጋች የፖለቲካ ፓርቲ አለ። አሁን ዳች ፓርላማ ውስጥ ሁለት መቀመጫ አለው። ፓርቲው መሬት ማንኛውንም የሰው ልጆች ፍላጎቶች ለማሙዋላት ትችላለች። ይሁን እንጂ የሰዎች ስግብግብነትን ለማሙዋላት አትችልም ብሎ ያምናል። እንደ ፓርቲው ከሆነ ለምሳሌ የእንስሳትና እንስሳት ተዋጽኦ እንዱስትሪ፤ 30% በተፈጥሮ ይገኙ የነበሩ የእንሥሣትና የእጽዋት ዘሮችን በማጥፋት ተጠያቂ ነው። ከብቶችንም ለማደለብም ሆነ የወተት ጎርፍ ለማምረት መኖ በገፍ ስለሚያስፈልገው፤ በዚህም ሳቢያ መሬት ከድሃ ገበሬዎች ስለሚቀማ፤ የአለም ርሃብ እየተባባሰ የመጣበት አንዱ ዋናው ምክንያት ከእንስሳትና እንስሳ ተዋጾእኦ እንዱስትሪ ተግባር ጋር የተያያዘ መሆኑን ያረጋግጣል። በተጨማሪም የእርድ እንሳሳት ሲታረዱ ህመም እንዳይሰማቸው ይደረግ ይላል። አንዳንድ እንስሳት በተለይ አሳማዎች ለእርድ ሲቀርቡ ያለቅሳሉ! አንጀት ይበላል ነገሩ።
አሜሪካውያት ሴቶች የምጥን ህመም ስለሚፈሩ ማደንዘዣ ይወጋሉ ይባላል። በአውሮፓ ግን ሴቶቹ ማማጡ በተፈጥሮ ያለ ነገር ስለሆነ፤ እናምጣለን! የምን ማደንዘዣ ነው… እቴ! ብለው የምጡን ህመም ጥርሳቸውን ነክሰው ይጋፈጡታል።
የሰው ልጅ የቆየ እምነትም ይሁን ዛሬ በሰለጠነው አለም እንደምናየው እንስሳትም ይሁን ሰዎች እንዳይሰቃዩ የሚደረጉትን ጥረቶች ጨረፍ ካደረግን ወደ ዋናው ጉዳያችን እንግባ።
በኢትዮጵያ መገዳደል አዲስ ነገር አይደለም። በታሪካችን ግዛት በማስፋፋት፣ የተለያዩ ጭቆናዎችን በመቃወም፣ በሃይማኖት ሳቢያ የደረሱ እልቂቶች አሉ። ቀይና ነጭ ሽብር ትልቅ ጠባሳ የጣሉቡን እልቂቶች ናቸው።
አይኖችቻን ይጥፉ! እምቢ አናይም ካላልን፤ በህወሃት አገዛዝ በአማራ ላይ አላባራ ያለው ግድያ ግን ለየት ያለ ነው።

ኢህአዴግ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ አለመሳካቱን አመነ

ኀዳር (አምስትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-ዘንድሮ የሚጠናቀቀው የኢህአዴግ የአምስት ዓመት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን የተለጠጠ ዕቅድ በግብርና ዘርፍ መዳከም ምክንያት ሳይሳካ መቅረቱን ኢህአዴግ ለመጀመሪያ ጊዜ  በይፋ አመነ፡፡
ኢህአዴግ «አዲስ ራዕይ» በተሰኘው በርዕዮተ ዓለም ልሳኑ የመስከረም- ጥቅምት 2007 ዓ.ም ዕትም ላይ የአምስት ዓመት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የአራት ዓመታት አፈጻጸም አስመልክቶ ባሰፈረው ሐተታ እንደጠቆመው ለጥጦ የያዘውን ዕቅድ ማሳካት እንዳልቻለ በማስቀመጥ አባላትና ደጋፊዎቹን አጽናንቷል፡፡
ግንባሩ ባለፉት አራት ዓመታት በግብርና ፣በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎት ዘርፎች አመርቂ ውጤት መገኘቱን በደፈናው ካስቀመጠ በሃላ ግንባሩ የተለጠጡ ዕቅዶችን አንግቦ የተነሳና ለማሳካትም ወቅቱ የፈቀደውን ያህል የተንቀሳቀሰ
ቢሆንም ከሞላ ጎደል መሠረታዊውን የዕድገት ምጣኔ እንጂ በተለጠጠ አኳሃን የነደፈውን ግብ ማሳካት ሳይችል መቅረቱን አምኗል፡፡ «በራሳችን ተነሳሽነት ለጥጠን ያስቀመጥነው ግብ ላይ ባለመድረሳችን ዛሬም የምንቆጭና ለነገ በእልህና በላቀ ወኔ መነሳሳት እንዳለብን የምንገነዘብ ቢሆንም በአራቱ ዓመታት በርብርብ የተመዘገበው ውጤት የሚያኮራ ነው» ሲል ይጠቅሳል፡፡

Wednesday, November 12, 2014

Ethiopia Court Requests Detailed Terror Charges Against

Bloggers [Bloomberg News]
By William Davison
An Ethiopian court asked prosecutors to amend charges so they specify the acts of terrorism that 10 bloggers and journalists are alleged to have been plotting, a defense lawyer said.
The order was made today at the Federal High Court in the capital, Addis Ababa, where nine out of the 10 accused are standing trial for collaborating with a U.S.-based opposition group, Ginbot 7, which is classified as a terrorist organization by Ethiopia’s government.
The charges “simply say these suspects organized themselves and designed terrorism without mentioning what kind of terrorism did they plot as defined under Article 3” of a 2009 anti-terrorism law, Ameha Mekonnen, the defense lawyer, said today in an interview in Addis Ababa.
Ethiopia is the second-worst jailer of journalists in Africa after Eritrea, its neighbor, according to the New York-based Committee to Protect Journalists. The U.S. has said previous convictions contravene freedom of speech rights protected by the constitution. Former newspaper editor Temesgen Desalegn received a 3-year sentence last month for publishing articles deemed to incite ethnic strife and the public to overthrow the government.
The court asked prosecutors to elaborate on the “clandestine” acts and the roles of each of theZone 9 group bloggers and journalists in plots, Communications Minister Redwan Hussien said by phone today. “They ordered the prosecutor to come up with the clarification,” he said.
Judges today rejected a second charge under the 2004 Criminal Code of inciting public revolt because it was covered by the first, Ameha said. The next hearing is on Dec. 3, he said.
Source: Bloomberg News

Monday, November 10, 2014

THE BRUSSELS ETHIOPIAN HISTORICAL MARCH!

November 10, 2014

Nightmare at the Woyyane Embassy

by Wondimu Mekonnen
Introduction
Nightmare at the Woyyane Embassy
The Woyyane (The TPLF) is a terrorist organisationi that is holding Ethiopia at ransom. Since the these criminals came to power, nothing changed in their wild behaviour. They were terrorists yesterday, they are terrorists today and unless they are stopped now, they wouldn’t change their behaviour in the future. The worsening brutality of the ethno-apartheid Woyyane (i.e. ethnic based black on black apartheid) regime has left Ethiopians with no option but to come together and resist tyranny of the worst kind in their history. As crackdown on the opposition members, journalists, religious leaders (both Christians and Muslims), and professional and human rights activists steps up, resistance is also rising to next level to defend the existence of oneself with more commitment and determination.
On 7th November 2014, this was the cause for the call of all Ethiopians to meet up in Brussels, the beautiful Belgian Capital City. The illegal and criminal abduction of Andargachew Tsege, General Secretary Ginbot 7 from Sana’a Airport was meant to scare-shock and silence the exiled community of Ethiopians to coil back into their shells but that was a wrong calculation on the part of the Woyyane. It proved otherwise.
The ethno-apartheid regime’s outrageous of series of abduction has ignited the fury of Ethiopians. They have been abducting the Oromo, the Ogadenese, the Gabellans from neighbouring counties. They have now upgraded that to the abducting an international air transport passenger. Will they get away with such blatant transgression of human rights? Their true colour is now exposed. Apart from the abduction, their murder squad has also been deployed in the cities of the World with diplomatic immunity. The recent brandishing of gun and shooting at demonstrators in Washington as we witnessed on 29 September 2014ii just a good example. That man has murdered single headedly during the 2005 election and before. Will we lie and day next day without resistance when they walk into our kitchen and murder us in exile tomorrow? No! Living under the yoke of fear is not life!

Sunday, November 9, 2014

እሥሩ ተጧጡፏል፣ አንድነት ምርጫ እንዳይወዳደር አገዛዙ ይፈልጋል

ግርማ ካሳ

ዜጎች መታሰራቸው እየቀጠለ ነው። በተለይም የአንድነት ፓርቲ አባላት (በጎንደር፣ በትግራይ፣ በመቱ፣ በአዲስ አበባ ፣ በወላይታ ….) ። ብዙዎች ከፍተኛ ደብደባ እየደረሰባቸው ነው። ሕወሃት ፣ በሕዝብ እንደተጠላ ስላወቀ የአንድነት ፓርቲ እንዲዳከም ወይም ከምርጫው ዉጭ እንዲወጣ እየሰራ ነው። አንድነት ሊያሸንፈው እንደሚችል ስላወቀ።

የድርጅቶች መተባበር አስፈላጊ በመሆኑ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር ተስማምቶ የቅድመ ዉህደት ስምምነት ፈርሞ ነበር። ሁሉም ነገር አልቆ ነበር። ሆኖም ምርጫ ቦርድ ወይንም አገዝዙ፣ ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ ዉህደቱን አስቁሞታል። ይኸው እስከአሁን ድረስ በአቶ አበባው ለሚመራው መኢአድ እውቅና አልሰጠም ብሎ መኢአዶችን ምርጫ ቦርድ እያጉላላቸው ነው።

የአንድነት ፓርቲ በቅርቡ በድርጅቱ ሕገ ደንብ መሰረት፣ አዲስ አመራር መርጦ መንቀሳቀስ መጀመሩም ይታወቃል። ሆኖ ምርጫ ቦርድ/ ሕወሃት ፣ በንድነት ዉስጥ አስርጎ አስገብቷቸው ከነበሩን በአንድነት እንዲራገፉ ከተደረጉት 2፣ 3 ግለሰቦች ጋር በመመካከር፣ እንደገና ለአዲሱ የአንድነት አመራር እውቅና አልሰጠም እያለ ነው። (የዛሬዉን ሰንደቅ ያንብቡ) ምናልባትም መኢአድ እና አንድነት ከምርጫዉ ሊያግዳቸው፣ አሊያም የነርሱን ሰርተፊኬት፣ ቅንጅትን ለአየለ ጫሚሶ እንደሰጠው፣ ለነ ማሙሸትና እና ለነ ዘለቀ ረዲ ሊሰጣቸውም ይችልም ይሆናል።

የሰላም ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ ታሰረ

የሰላምና የዕርቅ ሃሳብ መስበኩ "ወንጀል" ሆኖበታል
ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማስተባበርና በማቀራረብ እርቅ ለማስፈን እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት የመግባባት፣ አንድነትና ሰላም (ሰላም) ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አቶ ፋንታሁን የታሰረው ‹‹የሰላም ጥሪ›› በሚል ነጭ ሰንደቅ አላማ በማውረብለብና የማህበሩን አላማ የሚገልጹ፣ እንዲሁም ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለአገሪቱ ችግር የሚላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር የያዘ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በመበተን ማህበሩን በማስተዋወቅ ላይ በነበረበት ጊዜ እንደሆነ ታውቋል፡፡
በራሪ ወረቀቱ የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣ መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆምና መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ የሚመክሩ ሀሳቦች እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል፡፡
ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ የማህበሩን አላማና በህዝብ ላይ አሉ ያላቸውን ችግሮች ለህዝብ ሲያስተዋወቅ የተያዘው አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል እንደተከሰሰም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
አቶ ፋንታሁን እሁድ ጥቅምት 23 ሽሮ ሜዳ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትን ተይዞ ላዛሪስት በሚባለው ፖሊስ ጣቢያ ታስ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ (ምንጭ እና ፎቶ: ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia)

Saturday, November 8, 2014

አቶ በረከት ስምኦን የስልጣን መልቀቂያቸው ለጊዜው ይቆይ በሚል ውድቅ ተደርጓል::


-በውሳኔው የማይስማማ ከሆነ በሱና በቤተሰቡ በወዳጆቹ ስም የተመዘገበው ሃብት እንዲጣራ ተብሏል::
-ሳያገግሙ ስብሰባ እንዲመራ እና ሚዲያ ላይ እንዲቀርብ ታዟል::
Minilik Salsawi

የብአዲን/ኢሕአዲግ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ በረከት ስምኦን ያቀረቡት የስልጣን መልቀቂያ ለጊዜው በሚል ውድቅ መደረጉን ሆኖም በቅርቡ መልስ ይሰጥበታል ሲሉ የሕወሓት ባለስልጣናት መመለሳቸውን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::
አብዛኛውን ጊዜ ራሳቸውን ከቤት በማስቀመጥ እና በማዝናናት ያሳልፋሉ የተባሉት አቶ በረከት ስምኦን በልባቸው ላይ በተገጠመላቸው አርቴፊሻል መሳሪያ በጤንነታቸው ላይ ከባድ እክል እንደፈጠረባቸው እና ከወራት በፊት ሳኡድ አረቢያ ታክመው ቢመጡም ሊሻላቸው እንዳልቻለ እንዲሁም ባለፈው ሳምንት በድጋሚ ቢሄዱም ሆስፒታሉ ተስፋ እንዳስቆረጣቸው ሲታወቅ ከሕክምና መልስ ወደ ቢሯቸው የገቡት በጣት የሚቆጠር ቀናት እንደሆነ ታውቋል::
ይህን ሰሞን ስብሰባ መምራት አለብህ በሚዲያ መታየት አለብህ የሚል ግዳጅ ከሕወሓት ባለስልጣናት ወርዶላቸው የተደናበሩት አቶ በረከት ማገገም እንኳን ሳይችሉ በስራ መደራረብ እንዲሞቱ እየተደረገ ነው ሲሉ ከቤተሰባቸው አንዱ የሆኑት ሲናገሩ ተሰምቷል::አቶ በረከት በከፍተኛ ህመም ውስጥ እንዳሉ ሲታወቅ የሕወሓት ባለስልጣኖች የአዜብን ቡድን እንደመቱት ወዲያው በረከትንም ከጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ አሽቀንጥረው ካሳንቺስ አዲስ ቢሮ እንደሰጡት ሲታወቅ መገፋቱ እያንገበገበው በሽታውን እንዳባባሰበት ታውቋል::