Monday, November 24, 2014

ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት በቁጥር ‘S/2014/727’፣ በ ‘October 13, 20141 የወጣውን ሪፖርት በተመለከታል፤ ከሞረሽ ወገኔ ዐማራ የሲቪክ ድርጅት የተሰጠ መልስ

November 22, 2014
moresh-logo
ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት
Security Council Report One Dag Hammarskjöld Plaza 885 Second Avenue at 48th Street, 21st Floor New York, NY 10017
Telephone: 212-759-9429 Fax: 212-759-4038 Email: contact@securitycouncilreport.org
ኒውዮርክ፤
ከሞረሽ ወገኔ ዐማራ የሲቪክ ድርጅት
ሲልቨር ስፕሪንግ፣ ሜሪላንድ 20910
ዩ.ኤስ. አሜሪካ

ጉዳዩ፦ በቁጥር ‘S/2014/727’፣ በ ‘October 13, 20141 የወጣውን ሪፖርት ይመለከታል፤
  1. ሞረሽ ወገኔ ዐማራ የሲቪክ ድርጅት (ሞወዐድ)፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚኖሩት ፹፩ (ሰማንያ አንድ) ያህል ነገዶች እና ጎሣዎች (ብሔር/ብሔረሰቦች) መካከል በቁጥሩ ከጠቅላላው የአገሪቱ ሕዝብ ፴፭(ሰላሣ አምሥት) በመቶ ያህሉን ለሚይዘው እና ለሚደርስበት በደል የሚሟገትለት ቋሚ ጠበቃ ለሌለው የዐማራው ነገድ (ብሔር) ድምፅ ለመሆን የተቋቋመ የሲቪክ ድርጅት ነው። ድርጅቱ ከመስከረም ወር ፪ሺህ፭ ዓም (Sep 2012) ጀምሮ በተባበሩት የአሜሪካ ግዛቶች፣ በሜሪላንድ ግዛት ሕጋዊነት አግኝቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። ይህን ደብዳቤ ለተከበረው የፀጥታው ጥበቃ ምክር ቤት ለመጻፍ ያነሣሣንም፣ ከላይ በርዕሰ-ጉዳዩ ሥር በተጠቀሰው መግለጫ በገፅ ፴፩(ሰላሣ አንድ)፣ በአንቀፅ ፸፰(ሰባ ስምንት) የተገለፁት አረፍተነገሮች ፍፁም ከተሳሳተ መረጃ የተነሱ እና መሠረት የሌላቸው በመሆናቸው፣ በዘገባው የቀረቡትን አብዛኞቹን ዝርዝር ጉዳዮች ወደተዛባ አጠቃላይ ድምዳሜ ወስዷል የሚል ዕምነት ስላለን ነው።
  2. በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የትግሬ-ወያኔ (ሕወሓት) አገዛዝ የዐማራን ነገድ በአጠቃላይ በዘር ጠላትን ፈርጆ በመተዳደሪያ መርኃግብሩ ላይ ያሠፈረ ድርጅት ነው (አባሪ ፩ን ይመልከቱ)። ይህ ድርጅት ለ፲፯ (አሥራሰባት) ዓመታት በሽፍትነት፣ ለ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት ደግሞ በሥልጣን ላይ በቆየባቸው ጊዜያት በዐማራው ሕዝብ ላይ ያደረሰው የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት የወንጀል መጠን ሊስተካከለው የሚችለው በ፪ኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የናዚ ጀርመኖች በአይሁዳውያን ላይ የፈፀሙት ‘Holocaust’ ብቻ ነው። የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ዓለም በምትገኝበት ለሰብአዊነት ትልቅ ከበሬታ በተሰጠበት ዘመን፣ የወያኔ አገዛዝ ዐማራን በደመኛ ጠላትነት ፈርጆ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ሁሉ አቀፍ የጥፋት ዘመቻ በከፈተበትና እያንዳንዱን ተቃዋሚውን «ዐማራ ነው» እያለ በሚያሳድድበት ወቅት፤ ‘ግንቦት7’ ተብሎ የሚጠራው ድርጅት ዋና መሪዎች የዐማራው ሊሂቃን ናቸው ተብሎ በሪፖርቱ በዋናነት መጠቀሱ ነገዱን ለማጥፋት ቆርጦ ለተነሳው አገዛዝ «ድርጊትህ ትክክል ነው፣ ቀጥል ግፋበት» የሚል እንደምታ የሚያስተላልፍ መልዕክት የያዘ ሆኖ ስላገኘነው ድርጊቱ ከማሳሰብ አልፎ አሳዝኖናል።  ……  (ሙሉውን ከዚህ ላይ ያንብቡ, pdf )


No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.