Saturday, March 28, 2015

ለዓመታት የስለላ ሠራተኛና የአዲስ አበባ ቀጠና ኦፊሰር የነበረች የህወሃት አባል መክዳቷ ታወቀ።

10441451_642888442478281_4718393626091697818_n
በኢትዮጵያ የብሔራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎት መዋቅር ውስጥ ተመድበው የሚያገለግሉ የሰለላ ሰራተኞች በጽናት መስራት በማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸው ተሰማ። የጎልጉል ታማኝ የዜና ምንጮች አንዳሉት ድርጅቷ ህወሃትንና ታላቁን የአፈና ተቋም የስለላ ኦፊሰር የነበረችው የመክዳት ውጥኗ እውን የሆነላት ከስድስት ዓመት በኋላ ነው። በተደጋጋሚ ጊዚያት የዲፕሎማት ቪዛ እንዲሰጣት ፓስፖርቷን ለኢሚግሬሽን ብትልክም ያልተሳካላት ይህቺ የስለላ ኦፊሰር፣ በመጨረሻ የተሳካላት ስፔን አገር ለስለላ ስልጠና በማግኘቷ ነው።
አዲስ አበባ የሚገኙ ባልደረቦቿ “እርሷ ዕድለኛ ናት” በማለት ለጎልጉል ዘጋቢ እንዳሳበቁት፣ ኦፊሰሯ ስፔን አገር ከባልደረቦቿ ተለይታ ያመራችው ወደ አሜሪካ ነው። እዚያም እንደ ደረሰች እንደማትመለስ አረጋግጣለች። የትግራይ ክፍለ ሃገር ተወላጅና ታማኝ የህወሃት አባል የነበረችው የስለላ ሰራተኛ፣ ከቀበሌ ተነስታ ለከፍተኛ ሃላፊነት የበቃች ታማኝ ነበረች።

በብሔራዊ የደህንነት መዋቅር ውስጥ መሰላቸት፣ አለመተማመን፣ ጫና እንዲሁም ነጻ ሰዎች ሳይቀሩ የሚደረግባቸው ክትትል ጤና የነሳቸው ተበራክተዋል። በተለይም የህወሃት ያልተማሩ ነባር /አንጋፋ ባለሥልጣናት/ ታጋዮች የሚሰጡት ቅጥ ያጣ መመሪያና ወሬ ለቃሚዎቸ ከየመንደሩ ለብር እያሉ የሚያቀረቡት የሰላማዊሰዎችን ህይወት የሚያናጋ መርጃ ዕረፍት እንደነሳቸው የዜናው ምንጮች አመልክተዋል።
“በተለያዩ የሃላፊነት ደረጃ ተቀምጠው የሚያገለገሉ ባብዛኛው ደስተኛ አለመሆናቸው በገሃድ ስለሚታወቅና የመውጫው ቀዳዳ ስለተዘጋ” በሁሉም አቅጣጫ መሹለኪያ ፈላጊውና በሰላም መኖር የሚመኘው ክፍል እንደሚያይል ያመለከቱተ ዜና አቀባዮች “የኢህአዴግ ዙሪያ መለሱ ቆሽሾዋል፤ የእርስ በርስ መተማመኑም ኮስሷል” ብለዋል። በማያያዝም በርካታ አመራሮች አገር ለቅቀው መውጣት እንደማይችሉ አስታውቀዋል።ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ (ሚያዚያ 2፤2006ዓም/April 10,2014) “ከአገር መውጣት የማይችሉ ባለሥልጣናት በጭንቀት ውስጥ ናቸው፤ “አሁን ያለው ኢህአዴግ ላዩ በቀለም ቀቢ የተዋበ ይመስላል”” በሚል ዘገባ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ ለአንባቢያን እንዲረዳ ከዚህ በታች በድጋሚ አትመነዋል፡፡ ኢህአዴግ በሙስና ስም የ”ማጥራት ዘመቻ” ማካሄዱን ተከትሎ የተከሰተው አለመተማመንና እርስ በርስ በጥርጥር የመተያየት ችግር ካድሬውን ማስጨነቁ ተጠቆመ።
ኢህአዴግን ለመሰናበት የሚፈልጉ በርካታ ካድሬዎች “ለምን” በሚል የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመፍራት የግድ ፓርቲውን መስለው እንደሚኖሩ ተገለጸ።

Friday, March 27, 2015

“ጦር ሠራዊቱ ሕዝባዊ እምቢተኛነት ሲያይል የወያኔን መቃብር ይቆፍራል” – አርበኞች ግንቦት 7

የአርበኞች ግንቦት 7 ወቅታዊ መጽሐፍ

ጉዞአችን ወደ ነፃነት ነው!! መዳረሻችንም የነፃነት አደባባይ ብቻ ነው!!

አለማችን አንባገነን ስታስተናግድ ወያኔ የመጀመሪያው አይደለም። ዘረኛንም እንዲሁ …….. እኛም ስለነፃነት ብለን ለትግል ሰንነሳ የመጀመሪያዎቹ አይደለንም …… አለማችን እንደየዘመኑና እንደ የወቅቱ አንባገነኖች ያለ የሌለ የመሳሪያና ወታደራዊ ሀይላቸውን በመጠቀም ህዝብን በፍርሀት አሸማቀውና ረግጠው ለመግዛት ሲውተረተሩ በተደጋጋሚ ታይተዋል። በዚያው ልክ ህዝባዊ ሀይልና መመከት ተስኗቸው ሲንኮታኮቱ በተደጋጋሚ የታየ ወደፊትም አናባገነኖች እስከተከሰቱ ድረስ በህዝባዊ ሀይል ተጠራርገው መቀመቅ ሲወርዱ መታየቱ አይቀሬ ነው ። ህዝብ የወደደውን አስተዳዳሪ እንጂ ረግጦ ሊገዛው የሚፈልገውና አንባገነን ተቀብሎ አያውቅም ፤ዛሬም አልተቀበለም ፤ ነገም አይቀበልም ። ይህን በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ በተደጋጋሚና በጉልህ የሚታይ ግዙፍ እውነት መቼም ተቀብለውና ከታሪክ ተምረው ስለማያውቁ አሳፋሪው ውድቀታቸው በተደጋጋሚ ሲታይ አለ።
ginbot 7

ሀገራችን የአለማችን አካል እንደመሆኗ አንባገነኖች ተፈራርቀውባታል። አንባገነኖችም በህዝባዊ ሀይል ተጠራርገውባ ታል። ከደቡብ አፍሪካ ቀጥሎ ትልቅ ወታደራዊ ሀይል የነበረው የትናንቱ ደርግ እንደ እንቧይ ካብ ሲናድ ተመልክተናል። አንባገነኖችመናገር እንጂ መስማት የማ ችሉ፤ ማየት እንጂ ማስተዋል የተሳናቸው በመሆናቸው እነሆ ዛሬም የወያኔ ዘረኛው ቡድን ህዝባ ላነሳው የነፃነትና የፍትህ ጥያቄ ያለ የሌለውን ወታደራዊ ሀይል በጠራራ ጸሀይ በማሰለፍ መቼውንም ያልተቻለ ውን ህዝብን በሀይል አሸማቆ ለመግዛት መከራውን ሲያይ ይስተዋላል። ለዚህም ነው ….. ከሌላው የሀገራችን ክልሎች ከፍ ባለ ሁኔታ የህዝባዊ እንቢተኝነት እየታየ ባለበት ጎንደርና አካባቢው በሰራዊት ማጥለቅለቅ የተያያዘው።

ለሚነሱ ህዝባዊ ተቃውሞዎችና ህዝባዊ የመብት ጥያቄዎች የሚሰጡት ምላሾች እስር፤ አፈናና ግድያ ከሆነ ህዝባዊ እንቢተኝነትን ማስከተሉ አይቀሬ ነው። በእስር ፤በአፈናና በግድያ እንዲሁም በሰራዊት ሀይል ህዝብን በማሸማቀቅ በስልጣን መቆየት የሚቻል ቢሆን ደርግም ከቤተ-መንግስት ባልወጣ፤ ወያኔም ዛሬ ከቤተ-መንግስቱ ባልተንፈልለሰ ነበር። ይህ ደግሞ ሊያስተምር በተገባ ነበር።
እስከ ዛሬ የትኛውም አንባገነን ስርአት በሚተማመንበት የወታደራዊ ሀይል አማካይነት የመንኮታኮቻቸውን ሰአት በአንድ ሰኮንድ ማዘግየት የቻለ እንደሌለ ሁሉ ወያኔም ያለ የሌለውን ወታደራዊ ሀይል ሲያርመሰምስ ውሎ ቢያድር ውድ ቀቱን በአንድ ሰኮንድ ማዘግየት እንደማይችል በተለይ እንቢ ለነፃነቴ፤ እንቢ ለሀገሬ… ብለን ለትግል የተነሳን ሀይሎች በመረ ዳት፤ ይበልጡኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተቀጣጠለ ያለውን ህዝባዊ እንቢተኝነት ይበልጥ እያሰፋን የጀመርነውን የነፃነት ጉዞ ከነፃነታችን አደባባይ ለማድረስ ሌት ተቀን የመስራት ሀላፊነታችናና መወጣት ይገባናል።
በጎንደር የሚታየውን የአልገዛም ባይነት ትንቅንቅ በሌሎች ክልሎችም በማቀጣጠል፤ በደብረወርቅ የታየውን የመምህራን የስራ ማቆም አድማ ወደ ሌሎች አካባቢዎች በማስፋት፤ እንደ ድምፃችን ይሰማ ሁሉ ተቃውሞን ወደ እንቢተኝነት በማሸጋ ገር …… ወዘተ የነፃነታችንን ቀን ለማቅረብ መከፈል የሚገባውን መክፈል ይገባናል።
በደርግ ል የተነሳው እንቢተኝነት እያየለ ሲመጣ ያሰለፈው ሰራዊት ወያኔን አጅቦ የደርግን ቀብር እንደቆፈረለት ሁሉ ዛሬም በወያኔ ላይ እየተቀጣጠለ የሚገኘው ህዝባዊ እንቢተኝነት እየጠነከረ በመጣ ቁጥር የደረደረው ሰራዊት የወያኔን ቀብር ቆፋሪ ከመሆኑ እንደማኢመለስ ከቅርብ ጊዜ ታሪካችን በመማር ነፃነታችንን ለማስከበር የጀመርነውን የእንቢተኝነት ትግል በ መ ላው የሀገራችን ክፍሎች በማስፋትና በማቀጣጠል አይቀሬውን የወ ኔ ቀብር ለማቅረብ በአንድነት የነፃነት ጉዞውን እንቀ ላቀል። የጀመርነው የነፃነት ጉዞ መቆሚያው የነፃነታችን አደባባይ መሆኑን በተግባር ከምናሳይበት ወቅት ላይ እንገኛለንና በአንድነት እንነሳ!!!!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!!

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ከጥፋት የሚታደገው ብቸኛው መንገድ!!!

Amsalu
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሰሞኑን የተለያዩ ምሁራን በአማራ ስም የመደራጀትን አስፈላጊነት አጽንኦት ሰጥተው ጽፈዋል፡፡ አስቀድሞም ከፊሎቹ “ራሳችንን ማንነታችንን መሠረት አድርጎ እየተፈጸመብን ካለው ጥቃት ለመከላከል እንችል ዘንድ በራሳችን ብሔረሰብ በአማራ ስም የፖለቲካ ድርጅት ማቋቋም የግድ አስፈላጊ ነው” በማለት በአማራ ስም የፖለቲካ ድርጅት የማቋቋምን ጉዳይ አስፈላጊነት ያንጸባረቁ ነበሩ፡፡ አንዳንዶቹ ያልበሰሉትም ከዚህም አልፈው በተቀደደላቸው በር በመግባት የመገንጠልን ሐሳብ ያነሡም አሉ፡፡ እነኝህ ሁሉ አስተሳሰቦች ለኔ የሚያሳዩኝ ነገር ምንድን ነው? የወያኔና የሌሎች የጥፋት ኃይሎች የጎሳ ፖለቲካ ምን ያህል እንደሠራላቸው ስር እየሰደደ እንደሆነና ሳናውቀው የዚህ የጥፋትና ፀረ ኢትዮጵያ መርዘኛ የጥፋት ስብከት ሰለባ መሆናችንን ነው፡፡ እኔን የቸገረኝ ነገር ቢኖር እንዲህ ዓይነት አቋም ከያዝን በኋላ እኛን ከወያኔ የሚለየን ምን እንደሆነና የጎሳ ፖለቲካ ከሚያመጣው አላስፈላጊ ችግሮች አንጻር ከጎሳ ተኮር አደረጃጀት ርቀን በኢትዮጵያ ጥላ ስር ወይም ብሔራዊ አደረጃጀትን በመጠቀም ያሉብንን ችግሮች እንዳንዋጋ ምን እንደሚከለክለን ነው፡፡ የቸገረን ቆርጦ የሚታገል ታጋይ መጥፋት እንጅ የድርጅት ስም አይደለምና፡፡ አይበለውና አማራ እንደ ሕዝብ አማራነቱን ለማየት የኢትዮጵያን መነጽር አውልቆ የጎሳ መነጽር ያጠለቀ ለት ይህች ሀገር ያልቅላታል፡፡ የወያኔ ዓላማና ትግልስ ምን ሆነና? የአማራ ማኅበረሰብ በአማራ ስም ተደራጅቶ መታገል የማይፈልግበትና ይሄንን የሚጠላበት ከማንነቱ ጋር የተሳሰረ ምክንያትና አስቀድሞ የደረሰበት ላቅ ያለ የበሰለ አስተሳሰብ አለውና ይሄንን ቅርሱን የእናት አባት አደራውን እንድታከብሩለት እያሳሰብኩ ከብሔረሰብና ከእሱ ጋር ተያይዘው ስላሉብን ችግሮችና መፍትሔያቸው ላይ በማተኮር አምና የጻፍኩትን ይሄንን ጽሑፍ አሁን ከተቀሰቀሰው መነጋገሪያ አንጻር ወቅታዊ ሆኖ ስላገኘሁት እንድታነቡ እጋብዛቹሀለሁ፡-
ዛሬ እውነት እውነቱን እንቅጭ እንቅጩን እንነጋገራለን፡፡ እንዴ! ይሄ ሰው ከዚህ ቀደም ሲያወራልን የኖረው ቅጥፈት ነበር እንዴ? እንዳትሉ፤ አለ አይደል ይሄ መፏከቱን መሸራደዱን መበሻሸቁን ትተን እንደ ባለ አእምሮና ኃላፊነት እንደሚሰማው ዜጋ በንጹሕ በቅዱስ ልቡና ልዕልና ያለውን ሐሳብ አንሥተን እንወያያለን ለማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያ አምላክ ዐይነ ሕሊናችንን ያብራልን እዝነ ልቡናችንን ይክፈትልን አሜን!!
ሀገራችን ኢትዮጵያ የዘውግ ፖለቲካ (እምነተ-አስተዳደር) ወይም ብሔር ተኮር የሆነ ከፋፋይና አጥፊ የአገዛዝ ሥርዓት ውስጥ በግዳጅ እንድትዘፈቅ ከተደረገች 24ኛ ዓመታችንን ይዘናል፡፡ በዚህ ዘመን ውስጥ አንድነት የነበረው ሕዝብ በግድ ካልተነጣጠልክ፣ በጎሪጥ ካልተያየህ፣ እንደ አንድ ሀገር ሕዝብ ሁሉ ለእኛ ለእኛ ሳይሆን ለእኔ ለእኔ (ለብሔረሰቡ ብቻ) ካላልክ ተብሎ እየተወተወተ ወዶ ሳይሆን በግድ ይሄንን እኩይ አስተሳሰብን እንዲጨብጥ ተገደደ ተደረገም፡፡

Wednesday, March 25, 2015

ኑሮ በአዲስ አበባ (ነፃነት ዘለቀ – ከአዲስ አበባ)

ትናንት ሲያቀብጠኝ ከአንድ ጓደኛየ ሞባይል እነዚያ አይሲስ የሚባሉ ጉግማንጉጎች እነዚያን 21 ክርስቲያን የግብፅ ዜጎች በሊቢያ አንድ የባሕር ዳርቻ ላይ አንገታቸውን ሲቀሉ የሚያሣይ ቪዲዮ አየሁ – እስከመጨረሻው መዝለቅ አልቻልኩምና ግን ዋናው ባራኪ በግራ እጁ የያዘውን ጩቤ ወደ እኛ ወደተመልካቾቹ ዘርግቶ እያስፈራራ ሲዝት አጠፋሁት፡፡
addis-ababa-realethiopia-141

የሰው ልጅ በሰው ልጅ ላይ እስከዚህ መጨከኑ የሚያመላክተን ዋና ቁም ነገር የዚች ምድር ሰዎች የደረስንበት አጠቃላይ መንፈሣዊና ኅሊናዊ ኪሣራ ሊቀለበስ ወደማይችል ከፍተኛ የመጨረሻ ደረጃ መድረሱን ነው፡፡ ለምግብነት የተፈቀዱልንን እንስሳት እንኳን ስናርድ የሚዘገንነንና በዚህም ምክንያት የማናርድ ብዙ እንስፍስፍ ሰዎች አለን፡፡ ሰውን የሚያህል ክቡር ፍጡር ሊያውም በሚከተለው ሃይማኖት ምክንያት ብቻ በስለት አንገቱን ቀንጥሰው ጀርባው ላይ ሲያስቀምጡ ሊሰቀጥጣቸው ይቅርና በደስታ የሚፈነጥዙ “ሰዎች”ን በዚህ በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ስናይ በሰዎች ተፈጥሮ መለያየት እጅግ እንገረማለን፡፡

“A Message Signed with Blood, to the Nation of the Cross” ይላል የቪዲዮው መግቢያ፡፡ አስፈሪ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች በያዙት የመስፋፋት ሂደት ከቀጠሉ ሌሎቻችንም ይህ አስቀያሚ ዕጣ የሚቀርልን አይመስለኝም፡፡ ነገሩ “የፋሲካው በግ በገናው በግ ይስቃል” እንዳይሆን ያሰጋል – እየሆነም ነው እንጂ፤ ከመካከለኛው ምሥራቅ የተነሣ እሳት አፍሪካ ጫፍ ሊቢያና የመን ሲደርስ አያድርስ ብሎ ከመጸለይ ውጪ እኛስ ምን ዋስትና አለን? ይህን ቪዲዮ ከተመለከትበኋላ ለረጂም ጊዜ ሥራየን በአግባቡ መሥራት አልቻልኩም፡፡ ሰው ሆኖ የመፈጠር ዕዳ የቀሰቀሰብኝ የተስፋ መቁረጥ ስሜት መላ ሰውነቴን ወረረው – በአካልም፣ በመንፈስም፣ በኅሊናም እየኮሰመንኩ ስሄድ በምናቤ ይታየኝ ጀመር፡፡ አለመፈጠሬን የመረጥኩበት አንዱና ትልቁ አጋጣሚ ይህን ዘግናኝ ቪዲዮ በከፊልም ቢሆን ያየሁ ጊዜ ነው፡፡
ይህ በአስቀያሚነቱ ወደር የማይገኝለት ዓለም አቀፍ ክስተት በረድ እያለልኝ ሲመጣ ግን የሀገራችን አይሲስ ነጋዴዎች ታወሱኝና ስለነሱ አብዝቼ መጨነቅን ያዝኩ፤ ሁለቱ ተመሳሰሉብኝ፡፡ ደረጃውና ዓይነቱ ይለያይ እንጂ ጭካኔ ሁሉ መጠሪያውም ሆነ ጎራው ያው ጭካኔ ነው፡፡ እነዚህ ኢትዮጵያጵያውያን ኢይሲሶች የምላቸው በወያኔ የተፈጠሩ የዘመናችን ኅሊና ቢስ ነጋዴዎችንና ኑሯችንን ያመሰቃቀሉትን የሙስና አበጋዞችን ነው፡፡ ከወያኔ ቀጥለው የሀገራችንን የቀብር ሥነ ሥርዓት እያፋጠኑ የሚገኙት እነዚህ የቀን ጅቦች ናቸው፡፡
ወያኔ የዘራው ትልቁና መሠረታዊው ችግር የሀገር ብሔራዊ ስሜትን ማጥፋቱ ነው፡፡ ከዚህ በተያያዘም ሰብዓዊነትን ከሀገር አጥፍቷል፡፡ በምትኩ የተስፋፋው ዘረኝነት በወንዝ ልጅነትና በጎጥ፣ በቋንቋና በቤተሰብ መሳሳብ የጥቅም ትስስርን አንግሦ ጥቂቶች በሀብትና በሥልጣን ሽቅብ ሲመነደጉ አብዛኛው ሕዝብ እንጦርጦስ እየወረደ ነው፡፡ ወያኔ ዘረኝነትን በማስፋፋት ብቻ አልተወሰነም፡፡ ለሰው ልጅ ማኅበራዊ እንስሳነት እንደ አያያዥ ስሚንቶ ይቆጠሩ የነበሩ ሃይማኖትን፣ ባህልን፣ የሞራል ዕሤቶችን፣ መተሳሰብን፣ መፈቃቀርን፣ መቻቻልን፣ አብሮ መብላት መጠጣትን፣ … በጥቅሉ አንድን ሰው ሰው ሊያስብሉት የሚችሉ ሰብኣዊና ተፈጥሯዊ ክሮችን በጣጥሶ አንድያውን ሁላችንንም እንደራሱ ዐውሬ እያደረገን ነው፡፡ ከዚህ በሀገር ደረጃ ከታወጀብን የጥፋት ውርጅብኝ ለማምለጥ የምንውተረተር ዜጎች በጣም ጥቂቶች ነን፡፡ ዛሬ የብዙ ሰው መፈክር “ጅብ ከሚበላህ በልተኸው ተቀደስ” ሆኗል፡፡ አንድ ማስታወቂያ ነበር – “መጀመሪያ ራስህን አድን ለጫማው በኋላ ይታሰብበታል” የሚል፡፡ እኛም “‹ሀ› ራስህን አድን” በሚለው የራስ ወዳድነት መርህ እየተመራን አንዳችን አንዳችንን በልተን ልንጨረስ የቀረን ጊዜ ኢምንት ነው፡፡ በጩቤ አለመተራረድ ብቻውን ከአይሲስነት ተፈጥሮ ነፃ አያወጣም፡፡ “እሳት ካየው ምን ለየው” ነውና በምንም ይሁን በምን የዘመናችን የጭካኔ መገለጫ አይሲስ ሆኗልና ነጋዴዎቻችንና ጃዝ ባዮቻቸውም የንግዱ ዘርፍ አይሲስ ናቸው – ሥውር አራጆች፡፡
ኑሮ በአዲስ አበባ ምን ይመስላል? ሰዎች ለምንና በምን ብልሃት፣ እንዴትስ ብለው በሀብት ይከብራሉ? ብዙኃኑስ ለምን በሀብት ይደኸያሉ? የሀገራችን የሀብት ክፍፍል ምን ይመስላል?አብሮ መኖር ሲቻል መጠፋፋትን ምን አመጣው?
በአሁኑ ወቅት “ሀገራችን ወዴት እያመራች ነው?” ብሎ መጠየቅ ሞኝነት ይመስለኛል፡፡ ይልቁንስ “በጉዞዋ የት ደርሳለች? በብርሃን ፍጥነት እያስነካችው ያለችውን ጉዞ ጨርሳ ወያኔና ታሪካዊ ጠላቶቿ ወዳቀዱላት የመጨረሻ ግብ ለመድረስ ምን ያህል ጊዜ ይቀራታል?” ብሎ መጠየቅ ይመስለኛል አግባብ የሚሆነው፡፡ እንጂ ዕድሜ ለወያኔ ካሣለፍነው የሃያ አራት ዓመታት የጥፋት ጉዞ በመነሣት ወዴት እያመራን እንደሆነ ቁልጭ ብሎ የሚታይ ጉልህ ክስተት ነው፡፡
በአዲስ አበባ ስል በመላዋ ኢትዮጵያ እንደማለትም ቢቆጠርልኝ ደስ ይለኛል፡፡ ለውጥ ሊኖር ቢችልም እንኳን ያን ያህል የጎላ አይደለምና፡፡ እናም በሀገራችን ኑሮ በአሁኑ ወቅት እጅግ የሚሰቀጥጥ መሆኑን በመጠኑ እንመልከት፡፡
በደመወዝ ብቻ መኖር ከቀረ ብዙ ጊዜ አለፈን፡፡ ደመወዝ ስልህ ደግሞ ይግባህ – የመንግሥትንና በሲፒኤ ደንብ የሚተዳደሩትን ማለቴ ነው፡፡ ትላልቅ ደመወዞችን አይመለከትም፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከፈላቸው አሉና እነሱ የኑሮ ግርፋና ሰቆቃው አይነካቸውም፡፡

Wednesday, March 18, 2015

“አማራንና አማርኛን ማጥፋት የህወሃት ፕሮግራም ነው”

አማርኛ ተናጋሪዎችን የማመናመን፣ የማደህየት፣ የማራቆትና ክልላቸውን እያሳነሱ የማጥፋት እቅድ በህወሃት መርሃግብር ውስጥ የተካተተ ዋና ተግባር እንደሆነ ተገለጸ። አማርኛ ቋንቋንም ማሽመድመድ የዚሁ እቅድ አካል መሆኑ ተዘግቧል።
አቶ ገ/መድህን አርአያ ከኢሳት ሬዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ በህወሃት ፕሮግራም ገጽ 18 አካባቢ “አማራ የትግራይና የኤርትራ ህዝብ ጠላት እንደሆነ ተመልክቷል” ብለዋል፡፡ አያይዘውም አማራ ማጥፋት የቅስቀሳው ዋና መሳሪያ ቢሆንም የትግራይ ህዝብ አልተቀበለም ብለዋል። ቅስቀሳውን አንቀበልም ያሉ “የትግራይ ሸዋ” ተብለው መገደላቸውን ይፋ አድርገዋል።
በተለይ የድርጊቱ ዋና አስተባባሪ በማለት የጠቀሷቸው አቶ መለስ ዜናዊ፣ አቶ ስብሃት፣ አቶ ስዩም መስፍን፣ አቶ አባይ ጸሐዬን የጠቀሱት አቶ ገ/መድህን፣ በ1972 በሰሜን ጎንደር የዘር ማጥፋት ወንጀል መፈጸሙን አጋልጠዋል። በወቅቱ የተካሄደው ጭፍጨፋ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንደሆነም አመልክተዋል። “በሰላም እጃቸውን የሚሰጡ ወታደሮች እንኳ አማርኛ የሚናገሩ ከሆነ ይረሸኑ ነበር” ሲሉ እነ መለስ ያለቸውን በዘር ላይ የተመሰረተ ቆሻሻ አመለካከት አጋልጠዋል።
“ኢትዮጵያ የምትበተነው አማራ ሲጠፋ ነው” በሚለው የነመለስ ሃሳብ መተግበር የጀመረው ህወሃት አዲስ አበባ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑንን ያወሱት አቶ ገ/መድህን፣ ህወሃት ያሰማራቸው ከ350ሺህ በላይ ካድሬዎች ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ አማራዎች በተለያዩ ምክንያቶች እንዲጨፈጨፉ ማድረጋቸውን አመልክተዋል።
ብአዴንን “አማራን ለማጥፋት የተፈጠረ፣ ጸረ አማራ ድርጀት” ሲሉ የሰየሙት አቶ ገ/መድህን፣ አመራሮቹ የኤርትራና የትግራይ ተወላጆች መሆናቸውን በርግጠኛነት ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የተወከለው “በባንዳ ልጆችና የኤርትራ ተወላጆች ነው” ሲሉም ህዝቡ አደጋ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አባይ ወልዱን “የባሻ ወልዱ ልጅ ነው” በማለት የትግራይ ህዝብ በባንዳ ኤርትራዊ ልጅ እንደሚመራ ያመለከቱት አቶ ገ/መድህን፤ ብርሀነ ገብረክርስቶስ፣ ቴድሮስ ሃጎስ፣ ቴድሮስ አድሃኖም፣ በማለት በመዘርዘር የባንዳ ልጆች መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል።
“አማራው የሚኖርበትን መሬት በመውሰድ መሬቱን ያጠቡበታል፣ ከሌላው ክልል በማባረር የሚኖርበትን ክልል ያጠቡታል” ያሉት አቶ ገ/መድህን፣ ይህ የሚደረገው ከመጀመሪያው እንዲጠፋ የተወሰነበትን ህዝብ አጥብቦ በማፈን በችግር ለመግረፍና ለመቆጣጠር ተብሎ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዘር የማጥራት የህወሃት የቀደመ ድርጅታዊ መዋቅር እንደሆነ በማመልከት መለስን የጠቀሱት አቶ ገ/መድህን፣ “አማራውን ዝም ካልነው አያስቀምጠንም” የሚለው የመለስ መፈክር አካል የሆነው የቤኒሻንጉል ክልል ርምጃ የህወሃት ቤት ስራ እንደሆነ አረጋግጠዋል። አማራውን ፋታ ማሳጣት፣ ማንገላታት፣ ስነልቦናውን መግፈፍ ህወሃት በፕሮግራም ደረጃ የያዘው እቅድ ስለሆነ ወደፊትም እንደሚቀጥል አቶ ገ/መድህን ተናግረዋል።
“ሞት መፍራት አያስፈልግም። የተቀደሰ ሞት መሞት ክብር ነው” ሲሉ በቃለ ምልልሳቸው መጨረሻ የተናገሩት የቀድሞው የህወሃት የፋይናንስ ሃላፊ ህዝቡ ተባብሮ ህወሃትን ማስወገድ ካልቻለ ማፈናቀሉና መሰደዱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስጠንቅቀዋል።

Tuesday, March 17, 2015

ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ከአአ ዩኒቨርሲቲ ተባረሩ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. March 17, 2015)፡- በውጪ አገር ለሠላሳ ዓመታት የቆዩትና ለሰባት ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት የሰሩት ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ከስራ መባረራቸውን ገለጹ። ዶ/ር ዳኛቸው፣ ኢትዮጵያዊ ማለት መብቱ የሚረገጥ ማለት በመሆኑ፣ አሁን ገና ኢትዮጵያዊ ሆንኩ በማለት በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ገልጸዋል።
ዶ/ር ዳኛቸው ከዩኒቨርስቲው ከስራ የተባረሩበትን ምክንያት ሲገልጹ፤ የዩኒቨርስቲው የሴኔት ሕግና የቅጥር ውሌ ላይ በግልጽ እንደሰፈረው አንድ መምህር ለስድስት ዓመት በተከታታይ ከአስተማረ፣ ለአገለገለበት ዘመን የአንድ ዓመት የጥናትና ምርምር ዕረፍት (sabbatical leave) እንደሚሰጠው ተደንግጓል። ሆኖም በዚህ መነሻ በማድረግና የጡረታ ዕድሚዬ መድረሱን በማመካኘት እንድሰናበት አድርገውኛል ብለዋል።
ከዛ በፊት ለሦስት ወራት ደሞዝ ተከልክለው እንደነበር የገለጹት ዶ/ር ዳኛቸው፤ በተለምዶ ስድሳ ዓመት የሞላቸው መምህራን የውል ማራዘሚያ ጊዜ ይጠይቃሉ። እኔ የማውቃቸውና በተደጋጋሚ የተጨመረላቸው መምህራንም አሉ። በጣም አስገራሚና በግቢው አነጋጋሪ የኾነው ግን የእኔና የዶ/ር መረራ ጉዲና የውል ማራዘሚያ ጊዜ መከልከሉ ነው በማለት ምሬታቸውን ገልጸዋል።
ለዚህ ሁሉ መነሻ የሆነውና ከባለሥልጣናቱ ጋር አለመግባባት የተፈጠረበት ምክንያት፤ በፖለቲካ አመለካከታቸው ልዩነት እንደሆነ አልደበቁም። ከዩኒቨርሲቲው በመባረራቸው ብዙ ቢያዝኑም፤ ለሰባት ዓመታት ያህል ለማስተማር በመቻሌ ሙሉ የሆነ እውቀት ያገኙ ተተኪዎች ለማፍራት ስለበቃሁ አንጻራዊ ደስታ ይሰማኛል ብለዋል።
በሌላ በኩል ግን ከሌሎች ጥቃት ከደረሰባቸው ወጣቶች ዓይን ሲታይ የኔ መባረር ብዙም የሚያሳዝን አይደለም፤ እንደውም ለሰላሳ ዓመታት የት ነበርክ ብሎ የኢትዮጵያ ህዝብ ሳይወቅሰኝ ይሄንን ዕድል ሰጥቶ ስላሰራኝ ምስጋናዬ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። አሁንም ቢሆን የስራ ፍላጎት ቢኖረኝም በእንዲህ ዓይነት አገር የኔ ፍላጎት ብቻ ለስራ ብቁ ስለማያደርግ የወደፊቱን መናገር ያዳግታል፤ ሆኖም ሀገሬን ለማገልገል ምንግዜም ዝግጁ ነኝ ብለዋል።
ዶ/ር ዳኛቸው በዋናነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር ቢኾኑም፤ በሕግ ፋክልቲ፣ በሴንተር ፎር ሂዩማን ራይትስ፣ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም፣ በአምስት ኪሎ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፋክልቲ፣ በቴአትሪካል አርትስ እና በያሬድ የሙዚቃ ት/ቤትም እንዳስተማሩ ታውቋል።
ዶክተሩ በዩኒቨርሲቲው የቆዩበትን ጊዜ እና ዩኒቨርሲቲው የሚገኝበትን ተቋማዊ ኹኔታ በተመለከተ አንድ መጽሐፍ ለህዝብ እንደሚያቀርቡ ጠቁመዋል።

Monday, March 16, 2015

“ስሉሱ” ዞረ እንዴ?!

የምዕራቡ ሚዲያና ኢህአዴግ
ከጥቂት ሳምንታት ወዲህ ባልተለመደ ሁኔታ ኢህአዴግ ላይ ታዋቂ የዓለማችን ጋዜጦች የጀመሩት ተከታታይ ትችት፣ ማሳሰቢያና መፍትሔ ጠቋሚ ዘገባዎች መነጋገሪያ አጀንዳ ሆነዋል፡፡ ሚዲያዎቹ በዘገባቸው ኢህአዴግን ከቻይና አምባገነናዊና አክራሪ አገዛዝ ጋር አመሳስለዋል፡፡ ኢህአዴግ እከተለዋለሁ የሚለውን የኢኮኖሚ መርህ ከቻይና የተኮረጀ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ውጤቱም ሆነ መድረሻው ግራ የሚያጋባና የማይታወቅ እንደሆነ ዘግበዋል፡፡ ጋዜጦቹ ኢህአዴግን በሚንከባከቡት መንግሥቶቻቸው እና በራሱ ኢህአዴግ ላይ የሰላ ሒስ መሰዘንዘር መጀመራቸው የፖሊሲ አውጭዎችን አስተሳሰብ የሚያስቀይር ከመሆን አልፎ ኢህአዴግ ላይ “ስሉሱ” ዞሯል የሚያስብል እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡
ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም” በሚል ርዕስ የሰብዓዊ መብት ተመልካች የሆነው ድርጅት (ሂዩማን ራይትስ ዎች) ኢህአዴግ በሚያደርስባቸው ስልታዊ አፈና፣ ማስፈራሪያ፣ ህይወት የማጥፋት ዛቻ፣ … ምክንያት ኢትዮጵያ በጋዜጠኞች ላይ አፈና በማድረግ የቀዳሚነቱን ስፍራ መያዟን ባለ 76 ገጽ ዘገባ ካወጣ በኋላ በምዕራቡ ዓለም ያሉ ሚዲያዎች በኢህአዴግ አፋኝነት ላይ ጠንከር ያሉ ዘገባዎችን ማውጣታቸውን ይፋ እየሆነ መጥቷል፡፡
በዚህ ረገድ ቀዳሚውን ቦታ የወሰደው በዋሽንግቶን ዲሲ የአሜሪካ ፖሊሲና ሕግ አውጪዎችን አቅጣጫ በማመላከት የሚታወቀው “ዋሽንግቶን ፖስት” የዛሬ ወር አካባቢ የሰብዓዊ መብት ድርጅቱን ዘገባ ተተርሶ (የታፈነው የኢትዮጵያ ፕሬስ) “Ethiopia’s stifled press” በሚል ርዕስ አቋም የያዘበት ርዕሰ አንቀጽ ነው፡፡ ጋዜጣው እንዳለው በሟቹ መለስ የተጀመረው አፈና በቀጣዩ ሃይለማርያም አገዛዝም በይበልጥ እየከረረ መሄዱን ጠቁሟል፡፡ በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ከባላንጣዋ ኤርትራ እየባሰች መምጣቷን እንዲያው በተሻለ ሁኔታ ኤርትራ በጥር ወር ውስጥ በርካታ ጋዜጠኞችን ከእስር መፍታቷን ጨምሮ ገልጾዋል፡፡ ጋዜጣው ግልጽና የጠነከረ አቋም በወሰደበት በዚህ ርዕሰ አንቀጽ ማብቂያ ላይ አሜሪካ ለኢህአዴግ ዋንኛ ድጋፍ ሰጪ መሆኗን በመናገር በ2014 ለልማት ዕርዳታ በሚል 373 ሚሊዮን ዶላር መስጠቷን አስረድቷል፡፡ በአንጻሩ አሜሪካ ለዴሞክራሲና ለሰብዓዊ መብት ጥበቃ ማስፋፊያ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው ዕርዳታ በ2012ዓም 3.4ሚሊዮን ዶላር የነበረው በ2014ዓም ወደ 163ሺህ ዶላር ማሽቆልቆሉን ተናግሯል፡፡ ይህ የሆነበት ዋንኛ ምክንያት ኢህአዴግ ያወጣው የመያዶች ሕግ እንደሆነ ጋዜጣው ጨምሮ ገልጾዋል፡፡
ዋሽንግቶን ፖስት ርዕሰ አንቀጹን ሲጠቃልል ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ዕርዳታ በማግኘት ቀዳሚ እንደመሆኗ በዴሞክራሲ ዕድገት እየሄደችበት ያለው ጎዳና አጠያያቂ እንደሆነ እንደምታ ያለው ሃሳብ ከሰነዘረ በኋላ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) እና የኦባማ አስተዳደር እንዲሁም ባጠቃላይ ምዕራባውያን ማድረግ የሚገባቸውን በግልጽ አስቀምጧል፡፡ ስቴት ዲፓርትመንት በኢትዮጵያ እየተደረገ ባለው የሚዲያ አፈና ላይ ተቃውሞውን ማሰማት አለበት፤ ይህም ግን ከቃላት ማለፍ አለበት፤ የኦባማ አስተዳደር የሚሰጠውን ዕርዳታ ጋዜጠኞችና ጦማሪዎች እንዲፈቱ ከመጠየቅ ጋር ማቆራኘት አለበት (የማይፈቱ ከሆነ ዕርዳታ እስከመከልከል)፤ ሌሎች ምዕራባዊ ለጋስ አገራትም ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ማድረግ አለበት፤ ምዕራባዊ አገራት በአጠቃላይ ጋዜጠኞችን በማሰር በዓለም ታዋቂ ለሆነ አገዛዝ የሚያደርጉትን ዕገዛ ማቆም አለባቸው የሚል በዓይነቱ ተጠቃሽ የሆነና የምዕራቡ ዓለም በኢትዮጵያ ላይ የፖሊሲ ለውጥ እንዲያደርግ ግፊት የሚያደርግ ርዕሰ አንቀጽ ነበር፡፡
anuak woman aboboበቀጣይ የእንግሊዙ “ዘ ጋርዲያን” ኢህአዴግ በምዕራባውያን ዕርዳታ ከዓለም ባንክ የሚያገኘው 98ቢሊዮን ብር እንደነጠፈበት በመዘገብ “በመብት ረገጣ ምክንያት ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ከምትሰጠው ዕርዳታ አፈገፈገች” (British support for Ethiopia scheme withdrawn amid abuse allegations) በሚል ርዕስ ያወጣው ነው፡፡ ኢህአዴግን ከማንገስ ጀምራ በሥልጣን እንዲቆይ እንዲሁም በርካታ ድጋፍ ስትሰጥ የቆየችው እንግሊዝ እንዲህ ዓይነቱን እርምጃ ለመውሰድ መቻሏን ጋዜጣው በሰበር ዜና መልክ ማተሙ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው፡፡ ከተወሰኑ ጊዜያት በስተቀር በኢህአዴግ አገዛዝ ላይ የሰላ ሒስ ከመሰንዘር ከሚቆጠቡት የእንግሊዝ ሚዲያዎች አንጻር ዘጋርዲያን የወሰደው አቋም ለየት ያለ ነው፡፡ የእንግሊዙ የልማት ተራድዖ መ/ቤት “ኢትዮጵያ አድጋለች” በማለት ዕርዳታውን ከማቆም በማይተናነስ መልኩ ወደ 5በመቶ ማውረዱን ጋዜጣው ቢጠቅስም “ለዕድገቷ ማስረጃ” እንዲሆን ዜናውን ሲያትም በገዢነት ያወጣው የፎቶ ምስል በድንግዝግዝ ጸሃይ በአቧራ የተሰራ ቤት አቅራቢያ አቧራ ሲጠርጉ የሚታዩ ደካማ የአኙዋክ ሴትን ነው፡፡ የእርዳታው ገንዘብ ይሰጥ የነበረው መሠረታዊ አገልግሎቶችን ማለትም ትምህርት፣ ጤና፣ ንጹህ ውሃ አቅርቦት፣ መንገድ ሥራ፣ ወዘተ ለመሳሰሉ የዜጎችን ኑሮ ለሚያሻሽሉ አስፈላጊ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያነት ነበር፡፡

Thursday, March 12, 2015

የጎሳ ፌዴራሊዝም መርዝ በኢትዮጵያ (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

March 11, 2015
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የሀሰት እና የሸፍጥ የተውኔት መድረክ የተንጸባረቀበትን ህገመንግስት አርቅቆ እ.ኤ.አ ታህሳስ 8/1994 በማጽደቅ በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ጫነ፡፡ በህገ መንግስቱ ሰነድ የመጀመሪያ መግቢያ መንደርደሪያ ላይ እንዲህ የሚል ጽሁፍ ሰፍሮ ይገኛል፣ ”እኛ የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች…
1ኛ) የብሄሮችን፣ ብሄረሰቦችን እና ህዝቦችን የእራስን ዕድል በእራስ ለመወሰን፣
2ኛ) ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች የየእራሳቸውን አካባቢያዊ ግዛት እራሳቸው እንዲያስተዳድሩ እና የበለጸገውን እና የኩራታችን አሻራ የሆነውን የባህል ቅርሶቻቸውን በመያዝ በአንድነት እንዲኖሩ ለማስቻል፣
3ኛ) ለዘመናት ተንሰራፍተው የኖሩትን ፍትሀዊ ያልሆኑ ግንኙነቶችን ለማስተካከል፣ እና
4ኛ) አንድ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ በመፍጠር ዕድገትን ለማፋጠን ይህ ህገመንግስት ተዘጋጅቷል” ይላል፡፡
አነጣጥሮ ለመመልከት ደግሞ የአሜሪካ ህገ መንግስት በመገቢያው አንቀጾች ላይ የሰፈረው መንደርደሪያ እንዲህ ይላል፣ “እኛ የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ህዝቦች እንከን የሌላት ሀገርን ለመፍጠር፣ ፍትህን ለማስፈን፣ የሀገር ውስጥ ሰላም እና ጸጥታን ለማስፈን፣ የጋራ መከላከያችንን ለማጠናከር፣ የህዝቡን የኑሮ ደህንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የእኛን እና የመጭውን ትውልድ ነጻነት ለመጠበቅ ሲባል ለዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ይህንን ህገ መንግስት አዘጋጅተናል፡፡“
The Poison of Ethnic Federalism in Ethiopia’s Body Politic
የህወሀት ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ህገ መንግስት የኢትዮጵያን ህዝቦች እንደ ከብት መንጋ በአካባቢ በመለያየት ወይም ደግሞ በመበታተን እርስ በእርሳቸው የጎሪጥ በመተያየት የጥላቻ መንፈስ እንዲፈጠር እና ጎሳዊ፣ አካባቢያዊ እና መንደርተኛ አስተሳሰብ እንዲፈጠር በማድረግ የአንድነት ስሜት እንዳይኖራቸው እና አንዲት ጠንካራ ኢትዮጵያ እንዳትኖር በማድረግ በጎሳ ከፋፍሎ ለመግዛት የታለመ እና እንከንየለሽ አንድነትን ሳይሆን መለያየትን ለመፍጠር የተዘጋጀ የሸፍጥ ህገ መንግስት ነው፡፡ ህወሀት የኢትዮጵያን ህዝቦች በዘር፣ በቋንቋ፣ በባህል እና በአካባቢያዊነት ወይም በመንደርተኝነት በመከፋፈል ለዘመናት ተከባብሮ፣ ተዋዶ እና ተዋልዶ የኖረውን ህዝብ ማህበራዊ ትስስር፣ ፍቅር እና እርስ በእርስ መግባባት ሊመለስ በማይችል መልኩ ለዘመናት ለማጥፋት በማሰብ ይህንን እርባናየለሽ የሸፍጥ ህገ መንግስት አዘጋጅቶ በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ጭኖት ይገኛል፡፡

ሰበር ዜና – የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እየተቃጠለ ነው…

ብርቅዬውና በሀገራችን ከሚገኙ ብሄራዊ ፓርኮች አንዱ የሆነው የባሌ ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ እየተቃጠለ ነው፡፡ 
በደን ሀብቱ የሚታወቀው ይህ ፓርክ በተለይም ሼደን፡ ጡርጡራ፣ ቶዮ፣ ቴክአመሌና አበልጣሲም አካባቢዎች እሳቱ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰባቸው ካሉ አካባቢዎች ይጠቀሳሉ፡፡
በእሳቱ በከፍተኛ ደረጃ ጉዳት እየደረሰበት ያለው የአስታ ተክል በኢትዮጵያ ብቻ የምትገኘውን የቆቅ ዝርያ ጨምሮ በርካታ እንስሳትን ያስጠለለ ነው፡፡እሳቱ ዛሬም ለሶስተኛ ቀን መንደዱን ቀጥሏል፡፡ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የፓርኩ ባለሙያዎች እሳቱን ለማቆም እየታገሉ ነው፡፡

Tuesday, March 10, 2015

Ethiopia: Digital Attacks Intensify (Human Rights Watch)

March 9, 2015
(New York) – The Ethiopian government has renewed efforts to silence independent voices abroad by using apparent foreign spyware, Human Rights Watch said today. The Ethiopian authorities should immediately cease digital attacks on journalists, while foreign surveillance technology sellers should investigate alleged abuses linked to their products.
Ethiopia: Stop Using Anti-Terror Law to Stifle Peaceful Dissent
Independent researchers at the Toronto-based research center Citizen Lab on March 9, 2015, reported new attempts by Ethiopia to hack into computers and accounts of Ethiopian Satellite Television (ESAT) employees based in the United States. The attacks bear similarities to earlier attempts to target Ethiopian journalists outside Ethiopia dating back to December 2013. ESAT is an independent, diaspora-run television and radio station.
“Ethiopia’s government has over the past year intensified its assault on media freedom by systematically trying to silence journalists,” said Cynthia Wong, senior Internet researcher at Human Rights Watch. “These digital attacks threaten journalists’ ability to protect the safety of their sources and to avoid retaliation.”
The government has repressed independent media in Ethiopia ahead of the general elections scheduled for May, Human Rights Watch said. Many privately owned print publications heavily self-censor coverage of politically sensitive issues or have shut down. In the last year, at least 22 journalists, bloggers, and publishers have been criminally charged, at least six publications have closed amid a campaign of harassment, and many journalists have fled the country.

Monday, March 9, 2015

ምርጫውን ለህዝባዊ እንቢተኛነት እንዴት?

ዳዊት ዳባ
ህዘባዊ እንቢታ ማለት ዜጎች የስርአት ለውጥን ሆነ መብታቸውን ለማስከበር በብዙ ቁጥር ሆነው በጋራ አንድን ነገር ማደረግ ወይ አለማድረግ ነው። አለቀ። ብብዙ ቁጥር ተቃውሞ አደባባይ መውጣት በጋራ ልናደርጋቸው ከምንችላቸው በትንሹ ከሺ ነገሮች ውስጥ አንዱ የህዝባዊ ተቃውሞ አካል ነው። ተቃውሟችንን ለመግለፅ በጋራ ልናደርጋቸው የሚቻሉን ነገሮች ሁሌ የግድ ከባድም አጋላጭም መሆንም የለባቸውም። በይበልጥም ስንጀምረው።
Statement from 9 Ethiopian coalition parties
ማወቅ ያለብን አምላክ የሰውን ልጅ ሲፈጥር እስከነፃነቱ እንዲሆን አልሞ ነው። ሲፈጥረው ባስፈለገው ጊዜ አፈጣጠሩን በሙሉ ነፃነቱን ማስጠበቂያ አድርጎ እንዲጠቀምበት ነው። ሀሰት የሚል ካለ ይህንን አፈጣጠሩን ነፃነቱንና መብቱን ማስከበርያ አድርጎ ሊጠቀምበት አይችልም ይበል። እኛም ኢትዬጵያዊያን ሰዎች ነን። የሰው ልጅ እንደመሆናችን ስሜታችንን ፤ አካላዊ እንቅስቅሴያችንን፤ ውስጣዊም ሆነ ውጫዊ አካላችንን ፤ድርጊታችንን፤ አኗኗራችንን፤ የማሰብ ችሎታችንን፤ ፍላጎችንን፤ድምፃችንን ብቻ ሁለንተናዊ አፈጣጠራችንን መጠቀሙን እናውቅበታለን አናውቅበትም ነው እንጂ ጉልበታሞችን ልክ ማስገቢያ ካምላክ የተሰጠ ሀይላችን ነው።
ነፃነቱን ገፋፊው አንድ ግለሰብ ሲሆን ተገፋፊው ይሰራል ያለውን አፈጣጠሩን ተጠቅሞ በመዝጋትም ሆነ ልክልኩን በመንገር እንደሁኔታው አናቱን በድንጋይ በመበርቀስ ነፃነቱንና ክብሩን ማስመለስ ይችላል። ነፃነቱን የቀማው መንግስት ሲሆን ግን ብቻውን ሆኖ አደባባይ ላይ ወጥቶ በመጮህ ሆነ ተኩሶ እንዳሰበው ተፅኖ ፈጣሪና ውጤታማ ትግል ለማካሄድ ሁሌ የተሳካ ላይሆን ይችላል። በወረደ ምሳሌ፤- አንድ ሰው ብቻውን አገዛዝን ለመታገያና ተቃውሞውን ለመግለፅ አስቦ እደጅ ቢፀዳዳስ። ሲጀመር እስከጭራሹ ለምን እንዳደረገውም ላይታወቅ ሁሉ ይችላል። ነግር ግን ነፃነታቸውን የተነፈጉ በሙሉ አንድ ቀን ወስነው እጅ ለእጅ ተያይዘው እደጅ ቢፀዳዱስ። ይህ በቀጥታ ነቅንቅ የሆነ ተቃውሞ መሆኑ ጥያቄ ውስጥ አይገባም። { አይዞን ምሳሌ ነው። ካስፈለገ ተባብሮ ማፅዳቱንም ቀጣይ የተቃውሞ አይነት ልናደርገውም እንችላለን }።

Tuesday, March 3, 2015

ክፉን ሰውና ክፋተኝነትን እንዴት እናውቃለን?

በ ይሄይስ አእምሮ
Pen
ርዕሴ በጣም እንዳይጮኽብኝ ፈርቼ እንጂ ላደርገው አስቤና ፈልጌም የነበረው “ሰይጣንና ሰይጣናዊነት እንዴት ይታወቃሉ?” የሚል ነበር፡፡ ይህ ጽሑፌ በዚሁ ተመሳሳይ ጉዳይ ዙሪያ ባለፈው ሰሞን በአንዳንድ ድረ ገፆች የወጣውን በሴቴኒስቶች የሰላምታ መለዋወጫ ምልክቶች ምስል የተደገፈ አነስተኛ መጣጥፍ የተከተለ  ነው፡፡ ከሁሉ በፊት ግን ቀጣዩን ሥነ ቃላዊ ትውፊት ለነገሬ መነሻነት ባስቀድም ደስ ይለኛል፡፡

የቸገረው ሰው ከገባበት የችግር ማጥ ለመውጣት የማያደርገው ነገር የለም፡፡ አንዲት ሴት፣ ልጅ መውለድ እምቢ ይላትና ለዐርባ አራቱም ታቦት ትሳላለች፤ በዚያም አልሆነላትም፡፡ በየጠንቋዩና በየደብተራው ቤትም ደጅ ትጠናለች፤ በዚያም አልሆነም፡፡ በየጠበሉና በየሀኪም ቤቱም ትንከራተታለች፤ አሁንም በዚያም አይሆን ይላታል፡፡ ቢጨንቃት ለሰይጣን ትሳላለች፡፡ ስለቷም “አንተ እንደኔው የእግዜር ፍጡር የሆንክ ሰይጣን ሆይ! ልጅ እወልድ ብዬ ብዙ ተሳልሁ፤ ወጣሁ ወረድሁ ግን አልሆነልኝም፡፡ አሁን ደግሞ ባንተ በኩል ልሞክር ወስኛለሁ፡፡ ስለዚህ እስከዛሬ ዓመት ድረስ ወንድ ልጅ ከነቃጭሉ ከሰጠኸኝ ራሴው ፈትዬ አንድ ቡልኮ በስለት አስገባልሃለሁ” የሚል ነው፡፡
የአጋጣሚ ነገር ሆነና ልክ ባመቱ የሰማ ሰምቷት አንድ ወንድ ልጅ ከነቅጭልጭሉ ትወልዳለች፡፡ ደስታዋም ከጣሪያ በላይ ይሆናል፡፡ ከአራስ ቤት ጀምራ ትፈትልና በክርስትናው ማግሥት ለሰይጣን የተሳለችውን ቡልኮ በዕውቅ ሸማኔ አሠርታ ዝግጁ ታደርጋለች፡፡ ነገር ግን ያላሰበችው ችግር ይገጥማታል፡፡ ሰይጣንን የት አግኝታ ትስጠው? ችግር እኮ ነው፤ አንዱ ሲሟላ አንዱ አይሟላም፡፡
በየመንደሩና በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን እየዞረች “የሰይጣንን ቤተ ‹ክርስቲያን› ያያችሁ ነይ ወዲህ በሉኝ” ብትል ማን ዐውቆት ያሳያት? ብዙ ትለፋለች፤ ትደክማለችም፤ ነገር ግን በክንዷ አንጠልጥላ የምትዞረውን ቡልኮ ወይም ጋቢ የሚረከባት አንድም ሰይጣን ይጠፋል፡፡
ችግሯን ያስረዳቻቸውና የገባቸው አንድ ብልህ ሽማግሌ ግን እንዲህ ሲሉ ይመክሯታል፡፡ “አንቺ ሴትዮ፣ ልጅ ለመውለድ ያደረግሽው ጥረት በውነቱ የሚገርምና ታይቶም ሆነ ተሰምቶ የማያውቅ ነው፡፡ አሁን ሰይጣንን ካላገኘሽውና ቤቱንም ካጣሽው በአማራጭነት እንዲህ አድርጊ፡- እሁድ ቀን ወደ አንዱ ቤተ ክርስቲያን ሂጂ፡፡ ከዚያም ማርገጃው አካባቢ ሽማግሌዎች ተሰብስበው የተጣሉ ወይም የተቀያየሙ ሰዎችን በሚያስታርቁ ጊዜ የሽማግሌ ቃል አልሰማም ብሎ ንቋቸው ከጉባኤው እመር ብሎ የሚወጣ ሰው ስታገኚ ‹በስምህ የተሳልሁትን ልሰጥህ ስፈልግህ ኖሬ ዛሬ ገና አገኘሁህ፤ ይሄውልህ ቡልኮህ› በይና ትከሻው ላይ ጣይለት፤ ሰይጣን ማለት ዕርቅና ሰላምን የማይወድና የማይፈልግ ነውና እዚያ ማርገጃው ላይ በሰው ተመስሎ ታገኝዋለሽ፡፡” ይላታል፡፡
‹ሞኝ የነገሩትን፤ ብልህ የመከሩትን› ነውና ያቺ ሴት እንደተባለችው ቤተ ክርስቲያን እየሄደች ያን መሳይ ሰው ታጠምድ ያዘች፡፡ አንድ ቀንም እንደድንገት ሃሳቧ የሚሣካበት ምቹ አጋጣሚ ይፈጠራል፡፡ አንድ ደመ ሞቃት ሰው የሽማግሌዎችን ምክርና ተግሣጽ እንዲሁም የማስታረቂያ ሃሳብ ንቆ “ደግሞ እናንተን ብሎ አስታራቂ! ቀልማዳ ሁላ፤ እኔ ነኝ ደግሞ ‹በድየሃለሁና ይቅር በለኝ ብዬ እሱ እግር ላይ የምወድቅ?› የወሬ ቋቶች! …” በማለት ተስፈንጥሮ ከጉባኤው ሲወጣ ታየዋለች፡፡ ይሄኔ በደስታ እየተፍነከነከች አፈንጋጭ ጎልማሣውን ጠጋ ትልና “እሰይ! እንኳን አገኘሁህ! አሁን ገና ገበያየ ሞላ! ለስንት ጊዜ ስፈልግህ ኖሬ ዛሬ ገና ተሳካልኝ፡፡ በል ስለትህን ተረከበኝ” ትልና ቡልኮውን እሰውዬው ትከሻ ላይ ትጥልለታለች፡፡