Thursday, March 12, 2015

ሰበር ዜና – የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እየተቃጠለ ነው…

ብርቅዬውና በሀገራችን ከሚገኙ ብሄራዊ ፓርኮች አንዱ የሆነው የባሌ ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ እየተቃጠለ ነው፡፡ 
በደን ሀብቱ የሚታወቀው ይህ ፓርክ በተለይም ሼደን፡ ጡርጡራ፣ ቶዮ፣ ቴክአመሌና አበልጣሲም አካባቢዎች እሳቱ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰባቸው ካሉ አካባቢዎች ይጠቀሳሉ፡፡
በእሳቱ በከፍተኛ ደረጃ ጉዳት እየደረሰበት ያለው የአስታ ተክል በኢትዮጵያ ብቻ የምትገኘውን የቆቅ ዝርያ ጨምሮ በርካታ እንስሳትን ያስጠለለ ነው፡፡እሳቱ ዛሬም ለሶስተኛ ቀን መንደዱን ቀጥሏል፡፡ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የፓርኩ ባለሙያዎች እሳቱን ለማቆም እየታገሉ ነው፡፡

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.