Tuesday, June 30, 2015

“ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ይጋቡ” ጠቅላይ ፍርድቤት

 የፈጣሪን ሥርዓት “ምድራዊ ፍርድቤት መለወጥ አይችልም”
 same sex wed
* “ፍቅር ፍቅር ነው” ኦባማ
ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ጋር ጋብቻ መፈጸም ይችላሉ፤ ለእነርሱ የጋብቻ ሠርቲፊኬት መከልከል ሕገመንግሥቱን ይጥሳል በማለት የአሜሪካው ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መጋባት እንደሚችሉ ወሰነ፡፡ ለጋብቻ ቅድስናና ክቡርነት የሚከራከሩ “የእግዚአብሔርን ሕግ ምድራዊ ፍርድ ቤት ይህን መለወጥ አይችልም” በማለት ውሳኔውን አጥብቀው ተቃውመዋል፡፡ በምንም መልኩ ይገለጽ ፍቅር ፍቅር ነው በማለት ፕሬዚዳንት ኦባማ ውሳኔውን ደግፈዋል፡፡
ዋናውን (ዓቃቤ ፍትህ) ጨምሮ ዘጠኝ የፍትህ ዳኞች የያዘው የአሜሪካው ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዚህ የሰዶማውያን ጋብቻ ላይ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ ጉዳዩ ከቀረበለት ጊዜያት ተቆጥረዋል፡፡ በአሜሪካ የፍትሕ ሥርዓት ምዕራፍ ከፋች የተባለለት ውሳኔ አርብ ዕለት ሲተላለፍ የፍትሕ ዳኞቹ በአምስት ለአራት በመወሰን ነው ያጸደቁት፡፡ ይህ ጠባብ ልዩነት የታየበት ውሳኔ ሲተላለፍ አምስቱን ደጋፊዎች ወክለው አስተያየታቸውን የጻፉት የፍትሕ ዳኛ አንቶኒ ኬኔዲ ናቸው፡፡ እርሳቸውም ሲጽፉ “ከጋብቻ አንድነት የሚበልጥ የለም፤ ምክንያቱምታላቅ የሆነ ፍቅር፣ ታማኝነት፣ መስዋዕትነትና ቤተሰብን ያካተተ በመሆኑ ነው፡፡ ሁለት ከመሆን ይልቅ አንድ በመሆን የሚገኘው ኅብረት ይበልጣል በማለት ሰዎች የጋብቻ ኅብረት ይፈጥራሉ” ብለዋል፡፡ ሲቀጥሉም “ይህንን ጉዳይ በተመለከተ አቤቱታቸውን ያቀረቡት እንዳሳዩት ጋብቻ ማለት ሞትን አልፎ የሚሄድ ፍቅር መሆኑን ነው፤ … እነዚህ ሰዎች የጋብቻን ክቡርነት ያቃልላሉ ማለት እነርሱን አለመረዳት ነው፤ እንዲያውን እነርሱ ጋብቻን እንደሚያከብሩ ነው በመማጸን የሚናገሩት፤ ጋብቻን በጣም ስለሚያከብሩ ነው ተፈጻሚነቱን በእነርሱ ህይወት ማየት የሚፈልጉት፤ ጥንታዊ ከሆኑ ተቋማት አንዱ ከሆነው ጋብቻ ተገልለውና በብቸኝነት ተኮንነው ላለመኖር ነው ተስፋቸው” በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ውሳኔውን ከተቃወሙት የአራቱን በመወከል አስተያየት የጻፉት ዓቃቤ የፍትሕ ዳኛው ዮሐንስ ሮበርትስ ናቸው፡፡ እርሳቸው ውሳኔው በርካታዎች ሊያስደስት ይችላል ካሉ በኋላ ሲጽፉ “አብላጫውን ድምጽ የሰጡት ውሳኔ በጥልቅ ልብን የሚነካና ተስፋ የሚያስቆርጥ ነው፤ ጋብቻ በአንድ ወንድ እና በአንዲት ሴት መካከል የሚፈጸም ኅብረት ነው የሚለው ዓለምአቀፋዊ ትርጉም በምንም ዓይነት መልኩ ታሪካዊ አጋጣሚ አይደለም፤ ጋብቻ በፖለቲካ ትግል፣ በግኝት መልክ፣ በበሽታ፣ በጦርነት፣ በሃይማኖታዊ ሥርዓተ ሕግ ወይም አንዳች የዓለምን ታሪክ ባናወጠ ኃይል የተከሰተ አይደለም፤ እንዲሁም ወንድና ወንድ ወይም ሴትና ሴት ተጋቢዎችን ለማግለል ተብሎ የተደረገ የቅድመታሪካዊ ውሳኔ ውጤትም አይደለም” ብለዋል፡፡ ሲቀጥሉም “ጋብቻ የተከሰተው ወሳኝ የሆነን ፍላጎት ለማሟላት ነው፤ ይህም ደግሞ ከእናትና አባት ልጆችን በመውለድ እነርሱን በተረጋጋ ሁኔታ ለማሳደግ ራስን አሣልፎ በመስጠት የህይወት ሙሉ ውሳኔ በማድረግ ነው” ብለዋል፡፡

Wednesday, June 24, 2015

Amnesty International Asks Ethiopia to Investigate Suspicious Murders and Human Rights Violations

June 24, 2015
The suspicious murder of opposition leaders and wide-spread human rights violations against opposition party members over the past few weeks raises questions about Ethiopia’s elections, said Amnesty International as the parliamentary poll results were announced yesterday.Amnesty International
The organization has also expressed concerns about the failure of the Africa Union Elections Observer Mission (AUEOM) and the National Elections Board of Ethiopia (NEBE) to properly monitor and report on allegations of widespread abuses before, during and after the election.
“Amnesty International has received a number of reports concerning the deaths of political opposition figures in suspicious circumstances, as well as of a pattern of human rights violations against political opposition parties throughout the election period. These reports must be investigated and perpetrators brought to justice,” said Michelle Kagari, Amnesty International’s deputy regional director for Eastern, Horn of Africa and the Great Lakes.
“It is unacceptable that these violations barely warranted a mention in reports released by official observers, including the Africa Union Elections Observer Mission and the National Elections Board of Ethiopia.”
In the run-up to the elections, more than 500 members of the Ethiopian Federal Democratic Unity Forum (EFDUF)/ Medrek – a coalition of opposition parties, including the Oromo Federalist Congress (OFC) were arrested at polling stations in Oromia region. Forty-six people were beaten and injured by security officers while six people sustained gunshot injuries and two were shot and killed. Gidila Chemeda of the Oromo Federalist Congress (OFC/Medrek) was shot and killed by police in Western Shewa zone, Dima Kege Woreda, Gelam Gunge Kebele of the Oromia region.
On June 15, 2015, the body of 27-year-old Samuel Aweke, a candidate with the Samayawi (Blue) party was found in one of the main streets of Dembre-Markos at around 7 p.m. Blue party officials believe his murder was politically motivated. A few days before his murder, Aweke published an article in his political party’s newspaper Negere Ethiopia criticizing the behavior of local authorities, the police and other security officials. His political party claims he received threats from security officers after the article was published. Witnesses at the scene where his body was found said his body had visible stab wounds and appeared to have been beaten with a blunt object.
A member of the Arena/Medrek political opposition party reported that its leader for Western Tigrai zone, Tadesse Abraha, 48, was accosted while on his way home on June 16, 2015 by three unknown people who attempted to strangle him. Abraha managed to escape, but collapsed and died shortly after reaching his home. According to his political party, Abraha had reported being threatened by local security officials shortly before his death.
On June 19, 2015, another member of Medrek was found dead 24 hours after he was arrested at his home by two police officers. Berhanu Erabu’s battered body was found near a river in Hadiya Zone, Soro Woreda (district) of Southern Ethiopia.
Amnesty International has documented these killings and is now calling on the Ethiopian Ministry of Justice, Federal Police Commission and the Ethiopian Human Rights Commission to investigate these apparent targeted killings of opposition political party leaders and ensure those responsible are brought to justice
Background:
Amnesty International sent a letter with preliminary recommendations to the AUEOM on May 21, 2015.
Amnesty International expressed its concerns about the state of human rights in Ethiopia and the impact the human rights context was having on the ability of Ethiopians to participate in the electoral process. The organization urged the AUEOM to monitor and report on human rights violations throughout the election period in its assessment of the conduct of the elections.
The ruling political party, the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) has been declared the winner of the elections.

Tuesday, June 23, 2015

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በወያኔ የታፈኑበትን አንደኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በኖርዌይ፣ ኦስሎ ተካሄደ

June 23, 2015
የግንቦት 7 ዋና ፀሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን የፀጥታ ሃይሎች ታግተው ለዘረኛውና አፋኙ የወያኔ ቡድን ተላልፈው የተሰጡበትን አንደኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በኖርዌይ ደረጃ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ በወጣቶች ክፍል አስተባባሪነት በጁን 23/ 2015 በእንግሊዝ ኢምባሲ ፊት ለፊት እልህና ቁጭት የተሞላበት ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።
Demonstration infront of British embassy in Norway, Oslo
በሰልፉ ላይ ከተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች የተገኙ በርካታ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በኖርዌጅያን የሰአት አቆጣጠር ከ13፡30 ስዓት ጀምሮ ታላቋ ብርታኒያ ለዜጋዋ አቶ አንዳርጋቸው ልዩ ትኩረት አድርጋ ከዘረኛው ወያኔ ነጻ በማውጣት ወደ ቤተሰቡ እንዲመለስ ለማሳሰብ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው የነጻነት ታጋዩን አንዳርጋቸውን በተመለከተ የተለያዩ መፎክሮችን አሰምተዋል።
በዝግጅቱ ወቅት ከተሰሙት መፎክሮች መካከል “አንዳርጋቸው የነጻነት ታጋይ እንጂ አሸባሪ አይደለም” አንዳርጋቸው ነጻ ይወጣ ዘንድ እንግሊዝ ግፊት ታድርግ”፣ “በአንዳርጋቸው ላይ ለአንድ ዓመት ሙሉ እየደረሰበት ያለው የስቃይና የመከራ ዘመን ይብቃ”፣ እንግሊዝ ዜጋሽ የት ነው?”፣ “እንግሊዝ! ዜጋሽ አደጋ ውስጥ ነውና ደህንነትና ጥበቃ ያዝፈልገዋል፣ የህግ ከለላም እንዲሁ” “አዎ! እኛ ሁላችን አንዳርጋቸው ነን!” ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ያስፈልገናል” በማለት ከፍተኛ ሀገራዊ ስሜት በተንጸባረቀበት መልኩ ጩኸታቸውን አሰምተዋል።
በመቀጠልም አርበኞች ግንቦት ሰባት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የታፈኑበትን አንደኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የተሰጠውን መግለጫ ለተሳታፊዎች በድምጽ ተነቧል። መግለጫውም የአቶ አንዳርጋቸው በወያኔ መታገት ንቅናቄው የበለጠ
እንዲጠነክርና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ውህደት በመፍጠር ትግሉን ወደፊት እንዲሄድ አድርጎታል እንጂ ወያኔ እንዳሰበው ትግሉ ወደ ኋላ እንዳልቀረ ይጠቅሳል።
በመግለጫው ማጠቃለያም በአቶ አንዳርጋቸው ላይ በአፈናው የተነሳ የደረሰው መከራ ስቃይ ብቻ ሳይሆን በአሁኑ ጊዜ ለፍትህ ፣ ለእኩልነትና ለነፃነት በመቆማቸው በወያኔ አረመኔዎች ቁም ስቅላቸውን የሚያዩ በርካታ ቁጥር ያላቸው ዜጎች ሰቆቃ የሚያበቃው የኢትዮጵያ ህዝብ ተባብሮ በሚያደርገው ሁለ ገብ ትግል በመሆኑ ማንኛችንም በአቶ አንዳርጋቸውም ሆነ በሌሎች ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት እንደራሳችን አድርገን የሚሰማን ወገኖች በሙሉ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከታፈኑበት አንድ አመት ወዲህ የተጀመረውን ተስፋ የሚሰጥ እንቅስቃሴ አጠናክረን ወደ ውጤት በማድረስ የመጪው ዘመን የህዝብ የፍትህ የእኩልነትና የነፃነት ተስፋ የሚለመልምበት የወያኔ አምባገነን ስርአት እድሜ የሚያጥርበት ዘመን እንዲሆን ሁላችንም የምንችለውን ሁሉ እንድናደርግ ወገናዊ ጥሪ አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የተዘጋጀውን ደብዳቤ በተወካዮች አማካኝነት ለኢምባሲው ከተሰጠ በኋላ የተለያዩ መፈክሮችን በማሰማት ዝግጅቱ በታቀደለት ስዓት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
Demonstration organized by DCESON
andargachew-demo-norway3
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ

Friday, June 19, 2015

“መሞቴ … የተሻለ ነው” አንዳርጋቸው

የዓረና/መድረክ አባል ታንቀው ተገደሉ
three
* “ልማታዊ ግድያውን” ተጠናክሮ ቀጥሏል
እየሠራሁ ነው ለሚለው ልማትና ግድብ “እንደጀመርን እንጨርሰዋለን” እያለ የሚፈክረው ኢህአዴግ በየእስር ቤቱ የሚያሰቃያቸው ወገኖች ቁጥር እንዳለ ሆኖ “ልማታዊ ግድያውን” አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ሰሞኑን በግፍ የተገደለው ሳሙኤል አወቀን ጨምሮ ማክሰኞ ዕለት የዓረና-መድረክ አባል የሆኑት አቶ ታደሰ አብርሃ ታንቀው መገደላቸው ተሰማ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በሚያዚያ ወር በእንግሊዙ አምባሳደር የተጎበኙት አንዳርጋቸው ጽጌ ለመሞት ደስተኛ እንደሆኑና ምናልባትም የተሻለ መሆኑን ተናገሩ፡፡
የአቶ ታደሰ አብርሃን አገዳደል በፌስቡክ ገጹ ያሰራጨው አምዶም ገብረሥላሴ በዚህ መልኩ አቅርቦታል፡-
አቶ ታደሰ አብርሃ የተባሉ የዓረና-መድረክ አባልና የምዕራባዊ ዞን የዓረና አመራር አባል ትናንት ማታ 09/10/2007 ዓ/ም በሶስት ሰዎች ታንቀው ተገደሉ።
tadesseአቶ ታደሰ አብርሃ በቓፍታ ሑመራ ወረዳ ማይካድራ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ በዘንድሮው ምርጫ ወቅት በቀበሌው አስተዳዳሪዎች፣ ካድሬዎች፣ የሚቀርቧቸው ሰዎች ከዓረና-መድረክ አባልነታቸው እንዲለቁ የተሸመገሉ፣ የተለመኑና በመጨረሻም ዛቻዎች ሲደርስባቸው እንደነበረ ይታወቃል።
አቶ ታደሰ ማታ 03:00 በሶስት ሰዎች አንገታቸው የታነቁ ሲሆን ሶስቱ ሰዎች ሙቷል ብለው የተዋቸው ቢሆኑም ህወታቸው እስከ 09:15 አላለፈችም ነበር። አደጋውን 3 ሰዎች እንደፈፀሙባቸው፣ በኪሳቸውም 300 ብር የነበረ ቢሆንም ሰዎቹ እንዳልወሰዱት ተናገረው ነበር።
የአቶ ታደሰ ሬሳ በሑመራ ሆስፒታል እንዳይመረመር የማይካድራ ፖሊስ ትራፊክ በዓረና አባላት ላይ ከፍተኛ ጫና የፈጠሩ ሲሆን የተለያዩ የመንግስት አካላትም ምርመራው እንዳይካሄድ የተለያዩ ጫናዎች እንደፈጠሩ አባሎቻችን ከስፍራው ገልፀውልናል። ሬሳው ወደ ሑመራ ወስዶ ለማስመርመር የሚጠቅም መኪና ለመከራይ ሲባል አባሎቻችን የተከራዩት ሞተር ሳይክል በፖሊስ ትራፊክ ተከልክሏል።
የአቶ ታደሰ አብራሃ ቤት አከራይና ሌሎች ሰዎች ከአደጋው በተያያዘ ጫና እየተፈጠረባቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። የአቶ ታደሰ አብራሃ ግድያ በሳምንት ውስጥ የወጣት ሳሙኤል አወቀን ጨምሮ ለሁለተኛ ግዜ በፖለቲከኞች ላይ የተፈፀመ ግድያ ሲሆን ከ2007 ዓ/ም በዓረና-መድረክ አባላት ለሁለተኛ ግዜ የተፈፀመ ግድያ ያደርገዋል።
ባለፈው ታህሳስ ወር የደቡባዊ ዞን የዓረና-መድረክ አስተባባሪና የማእከላዊ ኮሚቴ አባል የነበረው አቶ ልጃለም ኻልአዩ በአዲስ አበባ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች መገደሉ ይታወቃል። አቶ ታደሰ አብርሃ የ48 ዕድሜ ጎልማሳ ነበሩ።
“መሞቴ … የተሻለ ነው” አንዳርጋቸው
በሌላ በኩል ዘ ኢንዲፔንደንት የተሰኘው የእንግሊዝ ጋዜጣ እንደዘገበው በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ዜጋቸውን ለመጎብኘት በሄዱ ጊዜ የሰሙትንና ያዩትን ምስክርነት ለመ/ቤታቸውና ለአቶ አንዳርጋቸው ባለቤት መላካቸውን አስታውቋል፡፡ ዘገባው ለባለቤታቸው በተሰጠበት ወቅት እጅግ ስሜትን የሚረብሽና መንፈስን የሚጎዳ ይዘት ስላለው ከቤተሰባቸው ጋር ሆነው እንዲያነቡት የውጭ ጉዳይ መ/ቤቱ ለባለቤታቸው ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ ነበር፡፡
አምባሳደሩና አንዳርጋቸው የተገናኙት በእስር ቤት ሳይሆን የደኅንነት ባለሥልጣናት በተገኙበት ቦታ ነበር፡፡ “በአካላቸው ላይ የሚታይ ምንም ዓይነት ጉዳት የለም” ያሉት አምባሳደሩ ለብቻቸው በመታሰራቸውና ከዚያ ጋር ተያይዞ የሚደርስባቸው ስቃይ መንፈሳቸውንና ስነልቡናቸውን እንደጎዳው በዘገባው ላይ ተናግረዋል፡፡andargachew
ሪፖርቱ ሲቀጥልም በውይይታቸው ወቅት አንዳርጋቸው ለአምባሳደሩ “እውነቱን ለመናገር ለመሞት ደስተኛ ነኝ – ምናልባትም የተሻለና ሰብዓዊነት ያለው ነው” ብለው እንደነገሯቸው በዘገባቸው ላ አስፍረዋል፡፡ “መንግሥት ይገድለዋል ብዬ ለማመን ይከብደኛል” ያሉት አምባሳደሩ አንዳርጋቸው በፈቃድ የመሞትን (ዩታኔዥያ) አከራካሪነት ያስተውላሉ ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፡፡
ሰሞኑን ከታሰሩ አንድ ዓመት የሚሆናቸው የ60 ዓመቱ አንዳርጋቸው የእስር ቤት ጠባቂዎቻቸው ራሳቸውን ይገድላሉ ብለው እንደሚፈሩ እርሳቸው ግን እስካሁን እንዳልሞከሩት ተናግረዋል፡፡
የአምባሳደሩን ሪፖርት ያነበቡት ባለቤታቸው ሪፖርቱን በጽሁፍ ሲያነቡ እንዴት እንደሰበራቸውና እንደጎዳቸው ለጋዜጣው ተናግረዋል፡፡ ለሌሎች የእንግሊዝ ዜጎች እንደተደረገው በእንግሊዝ መንግሥትም ሆነ በአምባሳደሩ ከዚህ የከረረ ጫና ባለመደረጉ ተስፋ የመቁረጥ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ባለቤታቸው ተናግረዋል፡፡
አቶ አንዳርጋቸው እንዲፈቱ የሚደረገው ጫና ሰሞኑን እየገፋ እንደመጣና ጉዳያቸው በተባበሩት መንግሥታት ልዩ ራፖርተር እየተመረመረ በመሆኑ ወደ እንግሊዝ እንዲመለሱ የሚደረገው ግፊት አንዱ አካል እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ የአንዳርጋቸው በእስር መቆየት ለኢትዮጵያና እንግሊዝ ግንኙነት መሻከር አስተዋጽዖ ያደርጋል በማለት የእንግሊዙ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት ለኢትዮጵያው እስካሁን በ13 የተለያ ጊዜያት እንዳነሳ ጋዜጣው አስታውቋል፡፡ አንዳርጋቸው የኤምባሲው ሰዎችም ሆኑ ጠበቃ እንዳያገኙ ተደርጎ በእስር የመቆየታቸው ሁኔታ አግባብነት እንደሌላው አሁንም መወትወታችን እንቀጥላለን በማለት የአምባሳደሩ ዘገባ ገልጾዋል፡፡
“መሞቴ … የተሻለ ነው” በማለት አንዳርጋቸው መግለጻቸው በምን ዓይነት የመንፈስ ጭንቀትና ስቃይ ውስጥ እንዳሉና ምን ያህል እረፍት ለማግኘት እንደሚፈልጉ የሚያመለክት እንደሆነ አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እየደረሰባቸው ያለውን እጅግ መራራ ስቃይም ሊስተዋሉ በሚችሉ ቃላት መግለጻቸው እየተሰቃዩ ከመኖር መሞትን እንዲመርጡ እንዳደረጋቸው ያሳያል፡፡
“በልማታዊ ግድያ” እና ማሰቃየት ላይ የተሰማራው ህወሃት/ኢህአዴግ ምርጫውን በግልጽ ከማጭበርበሩ አልፎ ቸሁ ደግሞ በተቀናቃኝ ፓርቲዎች አባላትና ደጋፊዎች ላይ እያደረሰ ያለው ጥቃት ወደ ግድያ ከፍ ማለቱ የዜጎችን ምሬት ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ ይወስደዋል የሚለው አስተያየት ከምንጊዜውም ይልቅ እየበረታ መጥቷል፡፡ ይህ ዓይነቱ ሁኔታና አሠራር ለዕርቅ በመንቀሳቀስ ላይ ለሚገኙ ወገኖች እጅግ ተስፋ የሚያስቆርጥና ሃሳባቸውን እንዲተዉ የሚያስገድድ እንደሆነባቸው በጉዳዩ ላይ ከተሰማሩት ለመረዳት ተችሏል፡፡

Thursday, June 18, 2015

Ethiopia Opposition Candidate Dies After Attack in Northwest

June 16, 2015
Samuel Awoke Opposition Candidate
Samuel Awoke (PHOTO: NegereEthiopia)
(Bloomberg) – An Ethiopian parliamentary candidate for the opposition Blue Party died after being assaulted in Debre Markos, a town in the country’s northwest, the group said.
Two people attacked Samuel Awoke, 29, with a club and knife as he returned home alone from a night out with friends, spokesman Yonatan Tesfaye said by phone Tuesday from the capital, Addis Ababa.
“We are trying to figure out who are the killers and the reasons,” he said, citing suspicions it was politically motivated. Ethiopian Communications Minister Redwan Hussien said in a text message that a suspect has been apprehended and the attack may have stemmed from a legal dispute.
Samuel reported previous death threats and a beating during campaigning for the polls that were held May 24, Yonatan said. The lawyer had been active in challenging election procedures and results in the Amhara region town, 295 kilometers (183 miles) northwest of the capital, he said.
All 442 of 547 federal seats announced so far were captured by the ruling Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front and allied parties.

Wednesday, June 10, 2015

ምርጫ ሲባል፣

መሳይና አስመሳይ
eth election 2015
ምርጫ ሲባል የነጻነት ዓየር አለ፤ ምርጫ ሲባል ተፎካካሪዎች አሉ፤ ምርጫ ሲባል ተፎካካሪዎች በእኩልነትና በነጻነት የቆሙበት መድረክ አለ፤ ምርጫ ሲባል የራሱን ፍላጎት በትክክል የሚያውቅና ከፍርሃት ነጻ የሆነ መራጭ አለ፤ ምርጫ ሲባል የተፎካካሪዎቹን እኩልነትና ነጻነት፣ የመራጮቹን እኩልነትና ነጻነት የሚያከብሩና የሚያስከብሩ ዳኞች አሉ፤ ምርጫ ሲባል የመራጮቹን ፍላጎት በትክክልና ያለአድልዎ የሚያሳይ ሰነድ የሚያዘጋጁ እግዚአብሔርን የሚፈሩ፣ ሕግን የሚያከብሩ፣ ለሕዝብና ለአገር የሚቆረቆሩ ሰዎች አሉ፤ ምርጫ ሲባል ይኸኛው ከዚህኛው ይሻለኛል ብለው የመወሰን ችሎታ ያላቸው ሰዎች አሉ፤ ምርጫ ሲባል መራጮቹ ተመራጮቹን ማገላበጥ አለ።
ታዲያ እኛ ምርጫ የምንለው ይህንን ሁሉ የያዘ ነው? ከዚህ በላይ ከተዘረዘሩት ውስጥ አንዱም እንኳን ቢጎድል፣ ምርጫ አንለውም፤ ምርጫ-መሳይ ልንለው እንችል ይሆናል፤ አንድ የሁለት ጓደኞች የቆየ ቀልድ ትዝ አለኝ፤ አንዱ ስሙ መሳይ ነው፤ ፊታውራሪ ነው፤ ሌላው ስሙ በፈቃዱ ነው፤ ሀኪም ነው፤ አንድ ቀን በፈቃዱ መሳይን ሲያገኘው በፊታውራሪነቱ ለማሾፍ ፊታውራሪ መሳይ አለ፤ መሳይን ጫን ብሎ፤ መሳይም ሲመልስ በዶክተርነቱ እያሾፈ ዶክተር በፈቃዱ ብሎ ዶክተርን ጫን ብሎ መለሰለት! የኛን ምርጫ-መሳይ ምን ብለን፣ እንዴት ብለን እናሹፍበት? ያውም ማሾፍ ከተፈቀደ! በባህላችን በጣም የተወደደ ምግብ አለ፤ ያንን ምግብ አቅርበው መሣሪያው ሲነፍጉ ሥጋውን ሰጥቶ ቢላዋውን መንሣት ይባላል፤ ንፉግነት ብቻ አይመስለኝም፤ ክፋትም አለበት፤ የደርግና የወያኔ ምርጫ-መሳዮች በአለማወቅና በንፉግነታቸው ይመሳሰላሉ፤ በክፋት ግን አይመሳሰሉም።