Tuesday, November 25, 2014

ወጣቱ ፖለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው የተናገረው

በግልፅ ከተቀመጠው አላማዬ ውጪ ሌላ የተደበቀ አላማ እስከሌለኝ የትም ቦታ ንፁህ አዕምሮ አለኝ ፡፡ንፁህ አዕምር ይዤ እኖራለሁ የመጨረሻው አማራጭ ወደ እስር ቤት መወርወር ሊሆን ይችላል እድል ፈንታችን ይሔ ሊሆን ይችላል ፡፡ይሔ ለኛ የተለየ አዲስ ነገር አይደለም በሰው ሁሉ ላይ ከደረሰው በእናንተ ላይ የደረሰ ምንም ነገር የለም ይላልና መፅሀፍ እኔም የተለየ ነገር ሊደርስብኝ አይችልም ፡፡ከቀድሞም ጀምሮ ኢትዮጵያ እንደዚህ ልጆቿን ስትበላ የኖረች ሀገር ናት፡፡አባቶቻችንም በተረት ይሉታል‹‹ኢትዮጵያ ሀገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ››እንስራ ለዚች ሀገር ባልን እንደዚህ አይነት ፈተናና መከራዎች መጋረጣቸው ያሳዝናል፡፡ቢያንስ ትውልዱ እንደዚህ አይነት ፈተና እንዳይገጥመው፤ልጄ እንዲህ አይነት ፈተና እንዳይገጥማት እኔ ይህንን ፈተና ተጋፍጬ ማለፍ አለብኝ፡፡ግን ሁሌም ዲሞክራሲያዊ መሆን አለብኝ ብዬ አምናለሁ ፡፡ፀረ ዲሞክራሲያዊ የሆነ አስተሳሰብን በፀረ ዲሞክራሲያዊ መንገድ መፍታት አይቻልም፡፡ፀረ ዲሞክራሲያዊ የሆነን አስተሳሰብ መፍታት የሚቻለው በዲሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ ነው፡፡በዲሞክራሲያዊ መንገድ መፍታት እንደሚቻል ደግሞ ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡

No comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.